1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሽታይንብሩክ አስተያየትና ትችቱ

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 25 2005

ሽታይን ብሩክ የጀርመን መራሄ መንግሥት ደሞዝ መሻሻል አለበት ፣ በመጪው ምርጫ የሚፎካከሯቸው የክርስቲያን ዲሞክራት ህብረት ፓርቲዋ እጩ መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ተዋቂ ፖለቲከኛ ለመሆን የበቁት ሴት በመሆናቸው ነው ማለታቸው በራሳቸው ፓርቲ አባላት ጭምር አስተችቷቸዋል ።

https://p.dw.com/p/17DPQ
German Chancellor Angela Merkel (L) listens as Peer Steinbrueck, candidate for Chancellor of Germany's social democratic SPD party, gives a speech at the Bundestag (lower house of parliament) on November 21, 2012 in Berlin. AFP PHOTO / JOHANNES EISELE (Photo credit should read JOHANNES EISELE/AFP/Getty Images)
ምስል Getty Images

አንጋፋው የጀርመን ሶሻል ዲሞክራቶች ፓርቲ ፖለቲከኛና የመጪው የጀርመን አጠቃላይ ምርጫ እጩ ተወዳዳሪ ፔር ሽታይን ብሩክ ሰሞኑን የሰጡት አስተያየት እዚህ ጀርመን እያነጋገረ ነው ። ሽታይንብሩክ የጀርመን መራሄ መንግሥት ደሞዝ መሻሻል አለበት ፣ በመጪው ምርጫ የሚፎካከሯቸው የክርስቲያን ዲሞክራት ህብረት ፓርቲዋ እጩ መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ተዋቂ ፖለቲከኛ ለመሆን የበቁት ሴት በመሆናቸው ነው ማለታቸው በራሳቸው ፓርቲ አባላት ጭምር አስተችቷቸዋል ። የቀድሞ የገንዘብ ሚኒስትር ሽታይንብሩክ ስለሰጡት አወዛጋቢ አስተያየትና አስተያየቱ ስለሚያሳድርባቸው ተፅዕኖ የበርሊኑን ወኪላችን ይልማ ኃይለ ሚካኤልን በስልክ ጠይቀናል ።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ