1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማሊያ ረሀብ መባባስ

ሰኞ፣ ሐምሌ 18 2003

በሶማሊያ የተከሰተው ረሀብ በየስድስት ደቂቃዎቹ ልዩነት የአንድ ሀጻን ህይወት እየተቀጠፈ ነው ሲል የጀርመን ዜና አገልግሎት ድርጅት DPA አተተ። በሶማሊያ የተከሰተውን ረሀብ ለመቃኘት የዶቼ ቬሌዋ ቤቲና ሩህል ሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ ተገኝታ የሚከተለውን ልካለች። ማንተጋፍቶት ስለሺ እንደሚከተለው አጠናቅሮታል።

https://p.dw.com/p/Rc2a
በረሐብ የተጎዳ አፍሪቃዊ ህፃን
በረሐብ የተጎዳ አፍሪቃዊ ህፃንምስል dapd
የርስ በርስ ጦርነቱ ፍዳ አሳሯን ያበላት የሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ ውስጥ በፈራረሱት ህንፃዎች መካከል የሚገኝ አነስተኛ ቦታ ነው። እመንገዱ ዳር በሚገኙት ባለሶስት ጉልቻ ምድጃዎች ላይ የተጣዱት አራት ድስቶች ይንፈቀፈቃሉ። በቅርበት ደግም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሶማሊያውያን አይኖች ከድስቶቹ ላይ ተክረዋል። ድስቶቹ ለዛሬ ለየት ባለ መልኩ ሩዝና የፍየል ስጋ እየበሰለባቸው ነው። ማንተጋፍቶት ስለሺ