«የሲዳማ አንድነት ፓርቲ» ሲአን ዳግም ምርጫ እንዲካሄድ ጠየቀ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 22 2013ማስታወቂያ
ተቃዋሚው «የሲዳማ አንድነት ፓርቲ» ሲአን በሲዳማ ክልል የተካሄደው ምርጫ የተለያዩ ሕገ ወጥ ያላቸው ተግባራት የተፈጸሙበት ነው ሲል በክልሉ ዳግም ምርጫ እንዲካሄድ ጠየቀ።የፓርቲው ሃላፊዎች ትናንት አዲስ አበባ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫና ለዶቼቬለ በሰጡት ማብራሪያ በምርጫ እለት ደረሱብን ያሏቸውን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አቤት ማለታቸውን አስታውቀዋል። ፓርቲው ምርጫው በተካሄደበት እለት ደረሱብኝ ባላቸው ኢሕጋዊ ተግባራትም ከምርጫው ራሱን ማግለሉንም ይፋ አድርጓል።የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተገኝቷል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ