1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሱዳኖች ጦርነት

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 4 2004

የሰሜንና የደቡብ ሱዳን ወታደሮች ሁለቱን ሐገራት በሚያዋስነዉ ድንበር የጀመሩትን ዉጊያ እንዲያቆሙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና የአፍሪቃ ሕብረት ጠየቁ።ሁለቱ ማሕበራት በየፊናቸዉ ባወጡት መግለጫ ሱዳኖች የሚያወዛግቧቸዉን ጉዳዮች በድርድር እንዲፈቱ አደራ ብለዋል።

https://p.dw.com/p/14cNg
Am 9.7.2011 wird Südsudan ein unabhängiger Staat.

የሰሜንና የደቡብ ሱዳን ወታደሮች ሁለቱን ሐገራት በሚያዋስነዉ ድንበር የጀመሩትን ዉጊያ እንዲያቆሙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና የአፍሪቃ ሕብረት ጠየቁ።ሁለቱ ማሕበራት በየፊናቸዉ ባወጡት መግለጫ ሱዳኖች የሚያወዛግቧቸዉን ጉዳዮች በድርድር እንዲፈቱ አደራ ብለዋል።ማሕበራቱ የደቡብ ሱዳን ጦር በሐይል ከያዘዉ አወዛጋቢ ግዛት ለቅቆ እንዲወጣም ጠይቀዋል።ሰሜን ሱዳን የደቡብ ጠላቷ የሚቆጣጠረዉን ግዛትዋን ካለቀቀ በሐይል ለማስለቀቅ ዝታለች።የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳት ሳልቫ ኪር ዛሬ እንዳሉት ግን ጦራቸዉ ከትናንት በስቲያ የያዘዉን ግዛት ለቅቆ አይወጣም።

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ