የሰሜን ኮርያ መሪ ሞት
ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 3 2004ማስታወቂያ
የሀገሪቱ ቴሌቪዥን እንዳመለከተው፡ የስድሳ ዘጠኝ ዓመቱ ኪም ዦንግ ኢል የሞቱት ባለፈው ቅዳሜ ጥዋት ሲሆን፡ በባቡር ከመዲናይቱ ወጣ ብለው ወደሚገኝ አካባቢ በመጓዝ ላይ እንዳሉ ነበር ሕይወታቸው ያለፈችው። የልብ ድካም ለኪም ዦንግ ኢል ሞት ምክንያት መሆኑን የቴሌቪዥኑ ዘገባ አክሎ አስታውቋል። የኪም ዦንግ ኢል ዜና ዕረፍት ከተሰማ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ትንሹ የኪም ዦንግ ኢል ልጅ የፓርቲው፡ የጦር ኃይሉ እና የሕዝቡ መሪ በመሆን ሟቹን አባታቸው እንደሚተኩ የሀገሪቱ ይፋ የዜና ወኪል አስታውቋል።
አርያም ተክሌ