የርዋንዳ መልሶ ግንባታ እና የሰብዓዊ መብት ይዞታዋ4 መጋቢት 2002ቅዳሜ፣ መጋቢት 4 2002የርዋንዳ መንግስት ከሙስና ነጻ በሆነበትና ከስምንት መቶ ሺህ የሚበልጡ ቱትሲዎች እና ለዘብተኛ ሁቱዎች የተገደሉበት የጎሳ ጭፍጨፋ ትቶት ካለፈው መዘዝ ማገገም በቻለበት ድርጊት የኤኮኖሚ ጠበብት እና ዲፕሎማቶች ያደንቃሉ።https://p.dw.com/p/MRWmየሩዋንዳዉ ፕሪዝደንት ፓዉል ካጋሜምስል APማስታወቂያበአሁኑ ጊዜ የርዋንዳ ህዝብ ወጣት ትውልድ ይበዛዋል። አብዝኃኑ ከሰላሳ ዓመት በታች መሆኑን እና በሀገር ግንባታው ስራም ላይ ማለፊያ አስተዋጽዖ በማድረግ ላይ መሆኑን ካጋሜ ሰሞኑን በብሪታንያ ለሮያል ኮመንዌልዝ ማህበረሰብ ባሰሙት ንግግር ላይ ገልጸዋል። አርያም ተክሌ/DW