1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመኢአድ መግለጫ

ማክሰኞ፣ ኅዳር 11 2005

መኢአድ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በሰጠው መግለጫ በተለይ በደቡብ ክልልና በአሶሳ አካባቢ አባላቶቹ ላይ የሚካሄደው የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል ። በአባላቶቹ ላይ ስለ ሚፈፀመው የመብት ረገጣ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም ሆነ ለሰብአዊ መብት ድርጅቶች ቢያሳውቅም ችግሩ አለመወገዱን መኢአድ ተናግሯል ።

https://p.dw.com/p/16mEE
Aerial view of Addis Ababa © derejeb #42996737
ምስል derejeb/Fotolia

ተቃዋሚው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት በምህፃሩ መኢአድ በአባላቱና በደጋፊዎቹ ላይ ተፈፀመ የሚለው የሰብአዊ መብት ረገጣ ና አፈና እንዲቆም ጠየቀ ።  መኢአድ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በሰጠው መግለጫ በተለይ በደቡብ ክልልና በአሶሳ አካባቢ አባላቶቹ ላይ የሚካሄደው የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል ። በአባላቶቹ ላይ ስለ ሚፈፀመው የመብት ረገጣ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም ሆነ ለሰብአዊ መብት ድርጅቶች ቢያሳውቅም ችግሩ አለመወገዱን የመኢአድ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ተናግረዋል ። መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝሩን ያቀርብልናል ።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ