1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመለያ ምርጫ በሴኔጋል

ቅዳሜ፣ መጋቢት 15 2004

ሴኔጋል ውስጥ በነገው ዕለት በሚደረገው ሁለተኛ ዙር ምርጫ በፕሬዚደንት አብዱላይ ዋድ አንጻር የሚፎካከሩት የተቃዋሚው ወገን ዕጩ ማኪ ሳል ጥሩ የማሸነፍ ዕድል እንዳለቸው ተሰማ።

https://p.dw.com/p/14QrQ
Opposition presidential candidate and former prime minister Macky Sall addresses journalists during a press conference at a hotel in Dakar, Senegal Wednesday, Feb. 29, 2012. Leading Senegalese opposition candidate Macky Sall said Wednesday that if he wins a presidential runoff next month he will revise the constitution to reduce the presidential term from seven to five years and that he will apply the shorter term to himself, as well as the two-term limit that is already present in the constitution.(Foto:Rebecca Blackwell/AP/dapd) Senegalese President Abdoulaye Wade addresses journalists during a press conference at the presidential palace in Dakar, Senegal Monday, Feb. 27, 2012. As votes were being tallied on Monday from Senegal's Sunday presidential election, leading opposition candidate Macky Sall declared that no candidate had gotten the necessary 50 percent, making a runoff "inevitable." (Foto:Rebecca Blackwell/AP/dapd)
ምስል dapd

ማኪ ሳል ከተቃዋሚው ወገን ብቻ ሳይሆን ካንዳንድ የሲቭሉ ማህበረሰብ ክፍልም ድጋፍ አግኝተዋል። አንድ የሀገሪቱ ርዕሰ ብሔር ከሁለት የሥልጣን ዘመን በላይ መቆየት እንደማይችል የሚያዘውን የሕገ መንግሥቱን አንቀጽ በመጣስ ለሦስተኛ ጊዜ በዕጩነት የቀረቡት የሰማንያ አምስት ዓመቱ አብዱላይ ዋድ በሥልጣን ለመቆየት የሚቻላቸውን ሁሉ ለመድረግ ቆርጠው የተነሱ ነው የሚመስለው። ይህ ጥረታቸውም ምናልባት በሀገሪቱ ሁከት ሊያስነሳ ይችል ይሆናል በሚል አንዳንዶች መስጋታቸው ባይቀርም፡ ዋድ የመጀመሪያውን ዙር ውጤት በመቀበላቸው፡ ካንዳንድ ተናጠል ግጭቶች በስተቀር የተፈራው ሁከት እንዳይነሳ ድርሻ ማበርከቱን የተቃዋሚ ቡድኖችንና የሲቭል ማህበረሰቦች የተጠቃለለበት ንቅናቄ ሀያ ሦስት የተባለው ድርህት ቃል አቀባይ አብደል አዚዝ ዲዩፕ አስረድተዋል።
« ምርጫው በሰላም ይካሄድ ዘንድ የሀገር አስተዳደሩ ሚንስቴር የፕሬዚደንት አብዱላይ ዋድ ደጋፊዎችን ጦር መሣሪያ ትጥቅ እንዲያስፈታ ጠይቀናል። ቆመጥ የያዙና የሼኽ ቤትዮ ቲውን የሀይማኖት ቡድን አባላት በመሆናቸው እነሱን መለየቱ አይከብድም። »
ሼኽ ቤትዮ ቲውን ፕሬዚደንት ዋድ አባል የሆኑበት የሙሪዴን ወንድማማችነት የሀይማኖት ቡድን መሪ ሲሆኑ፡ ቀስቃሽ በመሆንም ይታወቃሉ። በሙሪዴን ቡድን ድጋፍ ላይ ጥገኛ የሆኑት ፕሬዚደንት ዋድ መመረጣቸው እንደማይቀር በእርግጠኝነት ሲናገሩ መሰማታቸው ራሱ የነገውን ምርጫ ሂደት ትክክለኛነትን አጠራጣሪ አድርጎታል።
የነገው ምርጫ ከሁከት ነፃ እንዲሆን ከተፈለገ የተቃውሞው ወገንና ሲቭሉ ማህበረሰብ ግጭት በሚቀሰቅሱ ወገኖች ወጥመድ ውስጥ መግባት እንደሌለባቸው የፕሬዚደንቱ የዴሞክራቲክ ሶሻሊስት ፓርቲቃል አቀባይ ባባካር ጌይ አስገንዝበዋል።
ለሦስተኛ ጊዜ መመረጥ የሚፈልጉት አብዱላይ ዋድ ይህንኑ ዕቅዳቸውን የማይደግፉትን ወገኖች ለማረጋጋት ሲሉ ከጥቂት ጊዜ በፊት በሰጡት መግለጫ ላይ ቢመረጡ ቀጣዮቹን ሦስት ዓመታት ብቻ በሥልጣን እንደሚቆዩ አስታውቀዋል። ዋድ እነዚህኑ ሦስት ዓመታት ልጃቸውን ካሪም ወደ ሥልጣኑ ኮርቻ ለማምጣት ሊጠቀሙባቸው እንደሚችሉ ብዙዎቹ የሴኔጋል ዜጎች ሰግተዋል። በሴኔጋል ዜጎች ዘንድ እጅግ የተጠሉትና ከመንግሥት ካዝና ብዙ ገንዘብ ለግል ጥቅም አባክነዋል የሚባሉት ካሪም የመብራት ኃይል ኮርፖሬሽን ኃላፊ ሳሉ በሀገሪቱ ባለፈው ዓመት ለታየው የኮሬንቲ እጥረትና መጥፋት ተጠያቂ ናቸው በሚልም ይወቀሳሉ።
ይህ ሕዝቡ በመሪው ላይ የሚያሰማው ቅሬታ ሁሉ የተቃዋሚው ወገንና የሲቭሉ ማህበረሰብ ድጋፍ ያላቸውን የዋድ ተፎካካሪ ማኪ ሳል የመመረጥ ዕድልን እንዳመቻቸ የነፃነትና የስራ ፓርቲ አባልና የመንግሥታዊ ያልሆነው ለልማት የቆመው ድርጅት ሊቀመንበር አማኮዱ ዲዩፍ ገልጸዋል።
« የፕሬዚደንቱ ተፎካካሪ ሥልጣን ከያዙ፡ ሰፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥምረት ይፈጥራሉ። የሚከተሉት ፖሊሲም የተለያዩትን ፓርቲዎች ዕቅዶችን ያካተተ ይሆናል። ስለዚህ ይህ ፖሊሲያቸው ለሴኔጋል ሕዝብ ፍላጎት ትኩረት የሚሰጥ እንደሚሆን እንተማመናለን። »
በሙስና አንጻር በያዙት አቋማቸው ችግር ሲያጋጥማቸው ተቃውሞውን ወገን የተቀላቀሉት የማዕድንና የሀገር አስተዳደር ፡ በ ሁለት ሺህ ሰባት ደግሞ በጠቅላይ ሚንስትርነት ያገለገሉት የሀምሳ አንድ ዓመቱ ማኪ ሳል ካላሸነፉ ግን ዋድ በምንም ዓይነት መንገድ ሥልጣን መቆየት እንደሌለባቸው የዩኒቨርሲቲ መምህርና የሲቭል ማህበረሰብ አባል አብዱልአዚዝ ኬቤ አስታውቀዋል።
« ይህን ለማከላከል ቀጣዮቹን ሀያ አምስት ዓመታት ሙሉ ተቃውሞ ማድረግ ቢኖርብ፡ ማድረጋችን አይቀርም። ሀገሪቱን እንዲገዙ ዕድል አንሰጣቸውም። »
አንዳንዶች እንዲህ ቢሉም በኮትዲቯር በመጨረሻው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በኋላ በአሸናፊና በተሸናፊ ዕጩዎች መካከል የተፈጠረው ዓይነቱ ሁከት በሴኔጋል ይደገማል ብለው አያምኑም።

A security agent for Senegalese President Abdoulaye Wade wears a balaclava as he stands watch while Wade tours downtrodden suburban areas outside Dakar, Senegal Wednesday, March 21, 2012, ahead of Senegal's presidential run-off election. Senegal's aging leader will face his former protege Macky Sall in a runoff election on Sunday, March 25. Opposition leaders have united behind Sall in an effort to put an end to Wade's bid for a controversial third term as president. (Foto:Rebecca Blackwell/AP/dapd)
ምስል AP
Supporters of Senegalese President Abdoulaye Wade react as they wave to the passing president during a tour of downtrodden suburban areas outside Dakar, Senegal, Wednesday, March 21, 2012, days ahead of Senegal's presidential run-off election. Senegal's aging leader will face his former protege Macky Sall in a runoff election on Sunday, March 25. Opposition leaders have united behind Sall in an effort to put an end to Wade's bid for a controversial third term as president. (Foto:Rebecca Blackwell/AP/dapd)
ምስል AP

አርያም ተክሌ

መሥፍን መኮንን

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ