የለገጣፎ እና የለገዳዲ ገበሪዎች ስሞታ
ዓርብ፣ መስከረም 25 2005ማስታወቂያ
በኦሮምያ ክልል አዲስ አበባ ዙርያ የሚገኙ ለገጣፎ እና ለገዳዲ በተሰኙ የገጠር ቀበሌ ማህበራት ጤፍ እና ሌሎች ሰብሎችን እያመረቱ ይተዳደሩ የነበሩ ገበሪዎች፤ መሪታቸዉን ተመጣጣኝ ባልሆነ ካሳ አልያም ካሳ ሳይከፈላቸዉ ከቦታዉ ተፈናቅለዉ ችግር ላይ መዉደቃቸዉ ተሰምቶአል። ገበሪዎቹ ወደ ሚመለከተዉ ክፍል ሄደዉ አቤት ቢሉም መልስ ማጣታቸዉ ተነግሮአል። በአካባቢዉ የሚገኙ አንድ ሽ ያህል ገበሪዎች የፊርማ ድጋፍ ማሰባሰብ ስሞታቸዉን ለዉጭ መገናኛ ብዙሃን ማስተወቃቸዉ ተገልጾአል። በሐምሌ ወር 1998 ዓ,ም ለገጣፎ እና ለገዳዲ የተሰኙት የኦሮምያ ገጠር ቀበሌ ማህበራት በከተማነት መቆርቆራቸዉን ወኪላችን ዮሃንስ ገ/ እግዚአብሄር የላከልን ዘገባ ያመለክታል።
ዮሃንስ ገ/ እግዚአብሄር
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ