1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቤተ ክርስቲያን መፍረስ እና ውዝግቡ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 26 2009

የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ፣ታቦቱን ጨምሮ ሌሎች የአምልኮተ እግዚአብሔር መገልገያ ቁሳቁሶች በማይገባ ቦታ እንደተጣሉ ለዶይቼቬለ ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/2haap
Äthiopien Addis Abeba - Audienz beim Äthiopien Orthodox Tewahedo Kirche Patriarch Abune Mattias
ምስል DW/G. Tedla

የለገጣፎ ቤተ ክርስቲያን መፍረስ ያስነሳው ውዝግብ

 

በመቶዎች የሚቆጠሩ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮች  ለገጣፎ ይገኝ የነበረው የዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን አለአግባብ ፈረሰብን ሲሉ ቁጣቸውን እና ሀዘናቸውን  ገልጸዋል። የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ፣ታቦቱን ጨምሮ ሌሎች የአምልኮተ እግዚአብሔር መገልገያ ቁሳቁሶች በማይገባ ቦታ እንደተጣሉ ለዶቼቬለ ተናግረዋል። ቤተ ክርስቲያኑ የከተማውን ፕላን ግንዛቤ ውስጥ ሳይስገባ የተሰራ ነው ያለው የለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳዳር በበኩሉ ሲፈርስ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑን ለዶቼቬለ ገልጿል። መስተዳድሩ ቦታው ለቤተ ክርስቲያን የሚመጥን አይደለም ሲልም አስታውቋል። ሁለቱን ወገኖች ያነጋገረው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ኂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ