1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዓባይ: የግብጽ እና የኢትዮጵያ ንትርክ

ሰኞ፣ ሰኔ 10 2005

የዩጋንዳ ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ፣ ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ አገልግሎት በጥቁር ዓባይ ላይ ከምትሠራው ግድብ አኳያ ከግብፅ በኩል የተሰነዘሩ አስተያየቶች ያስቆጡአቸው መሆኑን በሰጡት መግለጫ ላይ አስታወቁ ።

https://p.dw.com/p/18qJs
A picture taken on May 28, 2013 shows the Blue Nile in Guba, Ethiopia, during its diversion ceremony. Ethiopia has begun diverting the Blue Nile as part of a giant dam project, officials said on May 29, 2013 risking potential unease from downstream nations Sudan and Egypt. The $4.2 billion (3.2 billion euro) Grand Renaissance Dam hydroelectric project had to divert a short section of the river -- one of two major tributaries to the main Nile -- to allow the main dam wall to be built. 'To build the dam, the natural course must be dry,' said Addis Tadele, spokesman for the Ethiopian Electric Power Corporation (EEPCo), a day after a formal ceremony at the construction site. AFP PHOTO / WILLIAM LLOYD GEORGE (Photo credit should read William Lloyd-George/AFP/Getty Images)
ምስል William Lloyd-George/AFP/Getty Images

ግብፅን ለመጉዳት የሚፈልግ ማንም አፍሪቃዊ ሀገር የለም ያሉት የዩጋንዳው መሪ፤ ሙሴቬኒ፣ ግብፅ ጥቁር አፍሪቃን መጉዳቷን መቀጠል አትችልም፤ የአሁኖቹ የግብፅ መሪዎችም ከዚያ በፊት የነበሩት ፣ መሪዎች የሠሩአቸውን ስህተቶች ሊደግሙ አይገባም ሲሉ ምክር መለገሣቸው ተመልክቷል።
«ከግብፅ የሚሠነዘሩ መግለጫዎችን፤ በጋዜጦች ተመልክቼአለሁ።የሚበረታታውን የኢትዮጵያን ሥራ--ወይም ለኤሌክትሪክ ማመንጫ የሚሆነውን የግድብ ሥራ በተመለከተ ማለት ነው--። መላው አፍሪቃም እንዲህ ዓይነት ተግባር ነው ማከናወን የሚኖርበት ። አንድ የሚታይ ውጤት፣--የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ፣ በባለሁለት አኀዝ መጠን በማደግ ላይ ነው የሚገኘው። ስለዚህ ይጠቅማል ብለን የምንመክረው፤ አዲሱ የግብፅ መንግሥትና አንዳንድ በዚያው በግብፅ የሚገኙ ትምክሕተኛ ቡድኖች፣ ያለፉት የግብፅ መንግሥታት የሠሩአቸውን ስህተቶች እንዳይደግሙ ነው።»
የዩጋንዳው ፕሬዚዳንት፤ ስሜታዊነትን ወደ ጎን በመተው በሠከነ አእምሮ መነጋገር፣ መወያየት እንደሚበጅ ከመጠቆማቸውም፤ ከጥቁር አፍሪቃ አንዳች ጉዳት ደርሶባት የማታውቀው ግብፅ፤ እርሷ ጥቁር አፍሪቃን መጉዳቷን ከአንግዲህ መቀጠል አትችልም ሲሉም አስገንዝበዋል።
««ስለዚህ ምክራችን፤ ከግብፅ የሚሠነዘሩት ትምክህተኛ መግለጫዎች እንዲቆሙና በዐባይ ወንዝ ተፋሰስ አገሮች ድርጅት በኩል ፣ በስሜት ሳይሆን በሰከነ አመለካከት መነጋገር፤ ውይይቶችንም ማካሄድ ተገቢ ነው።
ግብፅን መጉዳት የሚፈልግ አፍሪቃዊ የለም። እናም ፣ ግብፅ፣ ጥቁር አፍሪቃንና በምድር ሠቅ አካባቢ የሚገኙ የአፍሪቃ ሃገራትን መጉዳቷን መቀጠል አትችልም።»

ኢትዮጵያ በዓባይ ላይ የጀመረችዉ የግድብ ግንባታ፤ የውኃ ፍሰቱን የሚቀንስ ከሆነ ግብፅ በሁሉም አማራጮች እንደምትጠቀም ያሰማቸውን ማስጠንቀቂያ ኢትዮጵያ « የሥነ አዕምሮአዊ ጦርነት » ስትል በማጣጣል፣ በሚሰነዘርባት ማንኛውም ርምጃ አንፃር ራስዋን እንደምትከላከል በማስታወቅ የግድቡን ግንባታ ለአፍታ እንኳ እንደማታቋርጥ ገልጻለች። የሁለቱ ሀገራት እሰጣ ገባ እስከምን ይሆን?መፍትሄዉስ? በስዊድን የሚገኘዉ ዘጋብያችን ቴዎድሮስ ምህረቱ በስቶክሆልም በዓለም አቀፍ የዉሃ ተቋም ጠበብት የሆኑት አንቶን እርልን አነጋግሮ ዘገባ ልኮልናል


ቴዎድሮስ ምህረቱ
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ