ውዝግብ በኢትዮ ኦ ተ ቤተክርስቲያን
ሰኞ፣ ታኅሣሥ 22 2005ማስታወቂያ
የቀድሞው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አቡነ ጳውሎስ ካረፉበት ጊዜ አንስቶ የአዲስ ፓትሪያርክ ምርጫ በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ እንዳወዛገበ ነው። በሌላ በኩል አቡነ ጳውሎስ በህይወት ሳሉ አንስቶ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተጀመረው የእርቀ ሰላም ውይይት ቢቀጥልም ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ግልፅ አልተደረገም። በዚህ ሁኔታ ደግሞ ሰሞኑን ለሽምግልና ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ ከሄዱ ሁለት አባቶች አንዱ ከሃገር ተገደው ወደመጡበት መመለሳቸው ሌላኛው ደግሞ የደረሱበት እንዳልታወቀ አንዳንድ ዘገባዎች ወጥተዋል። በነዚህ ጉዳዮች ላይ የአዲስ አበባውን ዘገቢያችንን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔርን አነጋግራናል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ