1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ወጣቱና የታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝት

ዓርብ፣ ጥቅምት 1 2006

የአንድን ወይንም የራስን ሀገር፣ ቤተ መዘክር፣ ሀውልት፣ የህንፃም ሆነ ሌሎች ቅሪቶች እና የመሳሰሉትን በመጎብኘት ስለ ሀገር ታሪካዊ ቦታዎች እና ታሪክ ማወቅ ይቻላል። ለመሆኑ ወጣቱ ስለ ሀገሩ ታሪካዊ ቦታዎች ምን ያህል ያውቃል? ምን ያህልስ ማወቅ ይፈልጋል?

https://p.dw.com/p/19xZH
An Orthodox Christian walks to enter one of 11 monolithic rock-cut churches, ahead of Orthodox Easter in Lalibela May 4, 2013. REUTERS/ Goran Tomasevic (ETHIOPIA - Tags: RELIGION SOCIETY)
ምስል Reuters/Goran Tomasevic

ቤተልሔም ተሻገር እና ስያኔ አንለይ ሁለቱም አንድ የጋራ ዓላማ አላቸው። በተቻላቸው መጠን ስለ ሀገራቸው ታሪክ ማወቅና ታሪካዊ ቦታዎችን መጎብኘት ይፈልጋሉ። ፍላጎታቸውንም ዕውን በማድረግ ላይ ናቸው። አንዷ የሥራዋ ሁኔታ ይበልጥ ስላመቻቸላት ሌላኛዋ ደግሞ ሆን ብላ ጉዞዎችን በማቀድ እና በመተግበር ላይ ትገኛለች።

3.2 million year-old fossil "Lucy" is unveiled at Addis Ababa's National Museum on May 7, 2013. The fossil, discovered in 1974 in Ethiopia's Harar region, has returned home after a five-year tour of the U.S. It is the first time the skeleton has been on display in Ethiopia since 2000, and will be part of a temporary exhibition until May 13 before she is stored for research. Lucy is no longer the oldest-known member of the human family tree, but with 40 percent of her skeleton recovered, she is the oldest, most complete specimen of an early human species, standing about 3 feet, 6 inches tall and weighing approximately 60 pounds. She is named Lucy after the well-known Beatles tune, which her discoverers were listening to the day she was found. AFP PHOTO / JENNY VAUGHAN (Photo credit should read JENNY VAUGHAN/AFP/Getty Images)
የሎሲ( ድንቅነሽ) አፅምምስል Getty Images

የቤተልሔም ሥራ ከቢሮ አያስወጣም። የ28 ዓመቷ ቤተልሄም በተመረቀችበት የሂሳብ አያያዝ ሙያ ተሰማርታ አዲስ አበባ ውስጥ ትሰራለች። በተቻላት መጠን ግን የሀገሯን ታሪካዊ ቦታዎች ለመጎብኘት ዕረፍት ትወስዳለች። ይህም አስፈላጊ ነው ብላ ታምንበታለች። እንደ ጀርመን ባሉ አገሮች በተለይ በትምህርት ቤት ወቅት በቡድን በመሆን ታሪካዊ ቦታዎችን መጎብኘት በፍላጎት ብቻ ሳይሆን በግዳጅ የሚሰጥ የትምህርት አካል ነው? ይህ በኢትዮጵያ እንደ ትምህርት ቤቱ እና አስተማሪው ጥረት ይለያይ እንጂ በቡድን ታሪካዊ ቦታዎች መጎብኘት አለ። ቤተልሔም ትምህርት ቤት ሳለች ቤተ መዘክሮች መጎብኘቷን ታስታውሳለች። አብዛኛውን ጊዜ ለተማሪዎች ጊዜ ነፃ መሆናቸው ወይም ለመጎብኘት መጠነኛ ክፍያ ብቻ መጠየቃቸው ተማሪዎችን ያበረታታል ትላለች ቤተልሔም።

Residenz des äthiopischen Kaisers Fasilides udn seienr Nachfolger. Umgeben von einer 900 Meter langen Mauer wird die Stadt von Hindu- und Arab-EInflüssen geprägt. Jesuiten brachten den Barock-Stil. Copyright: DW/Azeb Tadesse Hahn
የፋሲል ግንብ ፤ጎንደርምስል DW/Azeb Tadesse Hahn

ሌላኛዋ ወጣት ስያኔ አንለይ ፤ በአዲስ አበባ ዮኒቨርስቲ የ2ኛ ድህረ ምረቃ ተማሪ ናት። በአሁኑ ሰዓት መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት ውስጥ በትርፍ ጊዜዋ የሥራ ልምምድ ታደርጋለች። ሥራዋም ኢትዮጵያን እየዞረች ከሀገሯ ታሪካዊ ቦታዋች ጋ እንድትተዋወቅ መንገድ ፈጥሮላታል። ወጣቷ በምታገለግልበት መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ የሥራ ድርሻዋ በትምህርት ላይ ያተኮረ ነው። ወደ ተለያዩ ከተሞች ስትሄድ ት/ቤቶችን መጎብኘት ከዋንኛ ሥራዋቿ አንዱ ነው። ስያኔ እንዴት አድርጋ ሥራ እና የሀገር ጉብኝቷን እንደምታዛምድ አጫውታናለች።

ሁለቱም ወጣቶች የሀገር ታሪካዊ ቦታዎችን ለማየት ስለሚያደርጉት ጥረት ነግረውናል። ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ