1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 ከጥቃት የተረፉት ጥገኝነት ጠያቂ

ረቡዕ፣ መጋቢት 18 2011

እዚህ ጀርመን ውስጥ በባየር ፌደራል ግዛት ጥገኝት የጠየቁ  የቀድሞ የኢትዮጵያዊ ጦር ሠራዊት ባልደረባ ከተቀነባበረ ጥቃት ለጥቂት መትረፋቸውን ለDW ገለፁ። ቴዎድሮስ በሚል ተለዋጭ ስም የሚጠሩት ሌተናል ኮሎኔል ጥቃቱ የተቀነባበረው  በቀድሞ የኢትዮጵያ መንግሥት የደህንነት ወይም የሥለላ ባልደረቦች መሆኑን ይናገራሉ።

https://p.dw.com/p/3FlDY
Radschnellwege im Großraum Nürnberg
ምስል picture-alliance/dpa/D. Karmann

ጉዳዩን ፖሊስ እየተከታተለ ነው

በ2008ዓ,ም ኢትዮጵያ ውስጥ በቀድሞው የደህንነት ኃላፊ የተሰጠኝን ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የኃይል ርምጃ የመውሰድ ትዕዛዝ ተግባራዊ ባለማድረጌ ድንገት ታፍኜ ከአራት ወራት በላይ በእስር ቆይቼ ነበር ይላሉ መጠሪያ ስማቸውን እንደለወጡ የሚናገሩት ስደተኛ። በመጀመሪያ ማዕከላዊ ከዚያም ወዳላወቋቸው ወደተለያዩ እስር ቤቶች ፊታቸው እየተሸፈነ በመዘዋወር ቁምስቅል እንደተፈፀመባቸው ይዘረዝራሉ።

እስር ላይ ሆነው ፍርድ ቤት በተወሰዱበት ወቅት ድንገት ባገኙት አጋጣሚ ለማምለጥ እና ከሀገር ለመውጣት የቻሉት በስደት ስማቸው ቴዎድሮስ የተባሉት ሌተናል ኮሎኔል የሊቢያን በረሃ፤ ቀጥሎም የሜዲትራኒያን ባሕር  አቋርጠው ጀርመን ቢገቡም  «አሳዳጆቼ» የሚሏቸው የቀድሞው የኢትዮጵያ መንግሥት የደህንነት ባልደረቦች ማስፈራራት እና ዛቻ አልተለያቸውም። በዚህም ሳይበቃ ከሰሞኑ ሊሰነዘርባቸው ከታቀደ የግድያ ሴራ ለጥቂት መትረፋቸውንም ያስረዳሉ።  ጉዳዩን በአካባቢው ለሚገኝ ፖሊስ በማመልከት ጥበቃ እና ክትትል እየተደረገላቸዉ መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል። ዝርዝሩን ከድምፅ ዘገባው ያድምጡ።

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ