1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኤፍሬም ሃጎስ እና የበጎ ፍቃድ ስራው

ዓርብ፣ ሰኔ 7 2005

የዛሬው የወጣቶች እንግዳ አዳጊ ወጣቶችን እያበረታታ ፤ አንድ ቀን የብሔራዊ ቡድን እግር ኳስ ተጫዋቾች ሆነው ለአገራቸው እንዲሳተፉ አስተዋፅኦ በማድረግ ላይ ይገኛል። ስለዚህ የበጎ ፍቃደኝነት ስራው ያጫውተናል።

https://p.dw.com/p/18p0V
Photo 3: Main title: "Speak and Listen to Them"... a campaign against the stereotype towards street children in Egypt Photo title: Two street children begging a man in a car for some money. Copyright: Ahmed Hamdy/Korrespondent der arabischen Redaktion Kairo Zulieferung :Chamselassil Ayari
ምስል DW/Ahmed Hamdy
Champions League match ball day before the UEFA Champions League final between Borussia Dortmund and Bayern Munich at Wembley Stadium in London, Britain, 24 May 2013. (Foto: picture alliance/dpa) / Eingestellt von wa
ምስል picture-alliance/dpa

ከነገ በስተያ(እሁድ) ለአለም እግር ኳስ ዋንጫ የአፍሪቃን ማጣሪያ ለማለፍ  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከደቡብ አፍሪቃ ብሔራዊ ቡድን ጋ አዲስ አበባ ውስጥ የመጨረሻ ግጥሚያውን ያደርጋል። የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ጨዋታ አፍቃሪዎች የሌሎች አገሮችን ግጥሚያዎች ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንንም የአፍሪቃ ዋንጫ በመሳሰሉ ግጥሚያዎች የሚያደርገውን ተሳትፎ እየተመለከትነው ነው።ይሁንና በአለም ታዋቂ የሆኑ ተጫዋቾችን ለማፍራት ብዙ መሰራት ይኖርበታል። የዛሬው የወጣቶች እንግዳ አዳጊ ወጣቶችን እያበረታታ ፤ አንድ ቀን የብሔራዊ ቡድን እግር ኳስ ተጫዋቾች ሆነው ለአገራቸው እንዲሳተፉ አስተዋፅኦ በማድረግ ላይ ይገኛል።

ኤፍሬም ሃጎስ ይባላል። ተወልዶ ያደገው አዲስ አበባ ነው። የልጅነት ህልሙ እግር ኳስ ተጫዋች መሆን ነበር። ነገር ግን ኤፍሬም በህይወቱ ብዙ ፈተናዎች ገጥመውት ስለነበረ ምኞቱን ዕውን ማድረግ አልቻለም። ይሁንና ሌሎች አዳጊ ወጣቶች ይህንን እድል እንዲያገኙ የበኩሉን በማድረግ ላይ እንደሆነ ገልፆልናል።

main title:displaced children in Morocco photo title:  moroccan displaced child in Rabat place and date:21/06/2012 Rabat Die Bilder haben wir von unserem Korrespondentin in Marokko siham ouchtou
ምስል DW/Ouchtou

ኤፍሬም በስምንት ዓመት ልጅ ሳለ ነው አባቱ የሞቱት። የሳቸውም መሞት ለዕሱ ፣ለታላቅ ወንድምና እህቱ ህይወትን ይበልጥ አከበደባቸው። ያኔም ኤፍሬም በልጅነቱ የጎዳና ህይወትን መተዋወቅ ነበረበት። ገንዘብም ለማግኛ ታላቅ ወንዱሙም ጫማ እንዴት እንደሚጠረግ አስተምሮት ከኑሮ ጋ ትግል ጀመረ።

ዛሬ ኤፍሬም 28 ዓመቱ ነው። በአገር አስጎብኚ እና በትርጉም ስራ በግሉ ይተዳደራል። ከዛ በፊትም ረዳት መምህር እና የእንግዳ መቀበያ ቤት ስራ አስኪያጅ በመሆን አገልግሏል። ይህም በጊዜ ህይወቱን ማቃናት በመቻሉ እንደሆነ ይናገራል። እሱም በበኩሉ አንድ ጥሩ አስተዋፅዎ ለማበርከት ይወስናል። ከልጅነቱ ጀምሮ ደስታ ይሰጠው የነበረውን እግር ኳስ ጨዋታ በበጎ ፍቃደኝነት የጎዳና ልጆችን ሰብስቦ ለመጫወትና ጎዳና ያሉትን አዳጊ ወጣቶች ለአጭር ጊዜም ቢሆን ለማስደሰት ከዛሬ ስምንት አመት በፊት ይወስናል። ያኔ እንደቀልድ የተጀመረው ስራ አድጎ ዛሬ ብዙ ወጣቶች ወደሚካፈሉበት የእግር ኳስ ፕሮጀክትነት ተቀይሯል ይላል ኤፍሬም፣ ኤፍሬም ይህንን በበጓ ፍቃደኝነት የሚያደርገውን ስራ ሲያከናውን ፈተናዎችም ገጥመውታል።  የወደፊት ትልቅ አላማም አለው።  የወጣቶች ማዕከል ማቋቋም ይፈልጋል። አጫውቶናል። ሁሉንም ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ