1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮ ኑረንበርግ ስለ ሮሙ ውድድር

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 18 2009

15ኛው በአውሮጳ የኢትዮጵያውያን ስፖርትና ባሕል ፌስቲቫል ከነገ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ድረስ በጣሊያን መዲና ሮም ከተማ ውስጥ ይከናወናል። ፌዴሬሽኑ ውስጥ በተነሳ አለመግባባት ግን ዘንድሮ በሮሙ ዝግጅት የሚሳተፉ የጀርመን ቡድኖች ሁለት ብቻ ናቸው፤ ኢትዮ ሽቱትጋር እና ኢትዮ ፍራንክፉርት ቡድኖች።

https://p.dw.com/p/2h8E1
Frankfurt ESCFE Festival
ምስል DW/S. Mantegaftot Sileshi

(Q&A) ESFCE-Nurenberg* - MP3-Stereo

15ኛው በአውሮጳ የኢትዮጵያውያን ስፖርትና ባሕል ፌስቲቫል ከነገ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ድረስ በጣሊያን መዲና ሮም ከተማ ውስጥ ይከናወናል። ፌዴሬሽኑ ውስጥ በተነሳ አለመግባባት ግን ዘንድሮ በሮሙ ዝግጅት የሚሳተፉ የጀርመን ቡድኖች ሁለት ብቻ ናቸው፤ ኢትዮ ሽቱትጋር እና ኢትዮ ፍራንክፉርት ቡድኖች። ኢትዮ ኮሎኝ ቡድን ትናንት ባቀረብነው የስፖርት ዝግጅት እንደገለጠው በውድድሩ የማይሳተፈው ፌዴሬሽኑ ውስጥ አለ ያለው ግልጽ ያልሆነ አሠራር የጠራ ባለመሆኑ ነው።

ፌዴሬሽኑ ለቀረቡበት ቅሬታዎች በትናንትናው የስፖርት ዝግጅታችን ምላሽ ሰጥቷል። የኢትዮ ኑረንበርግ የስፖርትና የባሕል ማኅበር ቡድን አባል አቶ ሳምሶን ተሰማ ቡድናቸው ለምን በሮሙ ዝግጅት እንደማይሳተፍ ዛሬ ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል። ማንተጋፍቶት ስለሺ አነጋግሯቸዋል።  
 

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ነጋሽ መሐመድ