1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮ-ቴሌኮም የ2011 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 16 2011

ኢትዮ-ቴሌኮም የ2011 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸሙን አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ት ፍሬሕይወት ታምሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት በሃገሪቱ በተከሰተው የኢንተርኔት መረብ መቆራረጥ ድርጅቱ ብዙ ሚሊዮን ብር ማጣቱን ገልጸዋል።

https://p.dw.com/p/3Mcub
PK des CEO von Ethio-Telecom Frehiwot Tamiru
ምስል DW/G. Tedla

ኢትዮ-ቴሌኮም የ2011 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸሙን አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ት ፍሬሕይወት ታምሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት በሃገሪቱ በተከሰተው የኢንተርኔት መረብ መቆራረጥ ድርጅቱ ብዙ ሚሊዮን ብር ማጣቱን ገልጸዋል። ሆኖም ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ ከ 40 እስከ 50 በመቶ የታሪፍ ቅናሽ አድርጎም ጭምር 36,3 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱ በመግለጫው ተጠቅሷል። የፋይበር መስመር መቆራረጥ፣ የቴሌኮም ማጭበርበር እና የኃይል አቅርቦት መቆራረጥ ኢትዮ ቴሌኮምን በበጀት ዓመቱ ውስጥ ያጋጠሙት ዋነኛ ተግዳሮቶች እንደሆኑም ተጠቁሟል። ከዶይቼ ቬለ «DW» ለቀረበላቸው ጥያቄ አጭር ምላሽ የሰጡት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ-ቴሌኮም ከዉጭ ድርጅቶች ጋር በአጋርነት ለመስራት ያለበትን ችግር አብራርተዋል። ጋዜጣዊ መግለጫውን የታደመው የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።


ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

   
አዜብ ታደሰ
ተስፋለም ወልደየስ