1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮጵያ ዉስጥ የታሰሩት የስዊድን ጋዜጠኞች አቋም

ረቡዕ፣ ጥር 2 2004

ኢትዮጵያ ዉስጥ አሸባሪዎችን በመደገፍና በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ወንጀል አስራ-አንድ አመት እስራት የተፈረደባቸዉ ሁለቱ የሲዊድን ጋዜጠኞች ምሕረት እንጂ ይግባኝ እንደማይጠይቁ አስታወቁ።

https://p.dw.com/p/13hf0
ምስል picture alliance/dpa

በየመጀመሪያ ስማቸዉ ስማቸዉ ማርቲንና ጆን ተብለዉ የሚጠሩት  የጋዜጠኞችን መግለጫ የጠቀሰዉ የሲዊድን ዜና አገልግሎት እንደዘገበዉ ጋዜጠኞቹ «ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጅም ጊዜ የቆየ» ያሉትን ይቅርታና ምሕረት ለመጠቀም ወስነዋል።ከጋዜጠኞቹ ጠበቆች አንዱ አቶ ደርበዉ ተመስገን እንዳሉት ግን ሥለ ደንበኞቻቸዉ ዉሳኔ የሚያዉቁት ነገር የለም። ጠበቃና የሕግ አማካሪ ደርበዉ ተመስገንን ነጋሽ መሐመድ በስልክ አነጋግሯቸዋል።

ነጋሽ መሀመድ
አርያም ተክሌ