1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አወዛጋቢው የዛራትሲን መጽሐፍ

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 25 2002

ትናንት እዚህ ጀርመን ገበያ ላይ የዋለው የጀርመን ቡንደስ ባንክ የቦርድ አባል የቲሎ ዛራትሲን መጽሐፍ ጀርመን ውስጥ አሁንም የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ እንደቀጠለ ነው ። “

https://p.dw.com/p/P17V
ምስል AP

ጀርመን ራሷን ለውደቅት እየዳረገች ነው” የሚል ሀሳብ የያዘው የዚህ መፀሀፍ ደራሲ የእስልምና ባሕል ጀርመን የሚኖሩ ሙስሊሞች ከህብረተሰቡ ጋር ተዋህደው እንዳይኖሩ እንቅፋት ሆኗል ሲሉ ተችተዋል ። ጀርመን ከሚኖሩ የውጭ ዜጎች በተለይ ሙስሊሞች ከህብረተሰቡ ጋር ባለመዋሀዳቸው ምክንያት ሀገሪቱን ከመጥቀም ይልቅ ሸክም እንደሆኑባት በመፀሀፋቸው ያካተቱት ሀሳብ ሙስሊሙን ህብረተሰብ በእጅጉ አስቆጥቷል ። ከጀርመንዋ መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል አንስቶ የጀርመን ፖለቲከኞችም የዛራትሲንን ሀሳብ ተቃውመው አስተያየታቸውን እየሰጡ ነው ።

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ

ሸዋዮ ለገስ