1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አቃቢተ ህግ ቤንሱዳ ቃለ መሃላ ፈፀሙ

ዓርብ፣ ሰኔ 8 2004

ጋምባያዊቷ ፋቱ ቤንሱዳ ለአለም ዓቀፉ የጦር ወንጀለኞች መዳኛ ፍርድ ቤት በእንግሊዘኛው ምህፃር የICC ጠቅላይ አቃቢተ ህግነት ዛሬ ቃለ መሃላ ፈፀሙ ። ዘ ሄግ ኔዘርላንድስ ውስጥ በተካሄደው የቃለ መሃላ ስነ ስርዓት ላይ የ51 ዓመትዋ ቤንሱንዳ የአቃቢተ

https://p.dw.com/p/15GCJ
Gambian war crimes lawyer Fatou Bensouda takes the oath to become the new prosecutor of the International Criminal Court (ICC) during a swearing-in ceremony at The Hague in the Netherlands June 15, 2012. Bensounda replaces Luis Moreno-Ocampo of Argentina. REUTERS/Bas Czerwinski/Pool (NETHERLANDS - Tags: CRIME LAW POLITICS)
ፋቱ ቤንሱዳምስል Reuters

ህግ ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል ። እጎአ ከ 2004 ዓም አንስቶ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት ሉዊስ ሞሬኖ ኦካምፖ አስረክበዋል ። ቤንሱዳ የአለም ዓቀፉ ፍርድ ቤት የመጀመሪያዋ ሴት ና አፍሪቃዊት አቃቢተ ህግ ናቸው ። የሥራ ዘመናቸውን ፈፅመው ዛሪ ሃላፊነታቸውን ለቤንሱዳ አስረክበዋል ። ቤንሱዳ የአለም ዓቀፉ ፍርድ ቤት የመጀመሪያዋ ሴት ና አፍሪቃዊት አቃቢተ ህግ ናቸው ። ለዚህ ሥልጣን የበቁትም ፍርድ ቤቱ የተመሰረተበትን የሮሙን ውል በፈረሙ 121 ሃገሮች ተመረጠው ነው ። አቃቢተ ህግ ቤንሱዳ የዘር ማጥፋት፣ የጦር እና በሰብዓዊነት ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች ክስ የተያዙባቸውን የ 7አፍሪቃ አገሮች 15 ጉዳዮችን የመርመር ሃላፊነት ተረክበዋል ። እጎአ በ2003 የተቋቋመው ዓለም ዓቀፉ ፍርድ ቤት እስካሁን 20 የእስር ማዘዣዎችን ቢቆርጥም እስካሁን የታሰሩት ግን 6 ተጠርጣሪዎች ብቻ ናቸው ። በፍርድ ቤቱ ከሚፈለጉት ውስጥ የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር አል በሽር ና የጌታ ተከላካይ ጦር የተባለው የኡጋንዳውየአማፅያን ቡድን መሪ ጆሴፍ ኮኒ ይገኙበታል ።

Fatou Bensouda, stellvertretende Chefanklägerin beim Internationalen Strafgerichtshof, Den Haag; Veranstaltung 21. September 2010, Berlin: "Alles was recht ist - Internationale Strafgerichtsbarkeit in Afrika"
ምስል DW

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ