1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አስተያየት በመገናኛ ብዙሃን ም/ቤት ምሥረታ

ዓርብ፣ ጥር 6 2008

ለበርካታ አመታት ሲወድቅ ሲነሳ የከረመው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ሰሞኑን ተመሥርቷል። ምክር ቤቱ በጋዜጠኞች መብትና የሥነምግባር ጉዳይ ላይ ትኩረት በማድረግ ችግሮች ሲፈጠሩ የማረምና የማስተካከል ኃላፊነት እንደሚኖረው ተነግሯል።

https://p.dw.com/p/1HeK9
Äthiopien Addis Abeba Medienrat
ምስል DW/G. T. Hailegirorgis

ከምሥረታው በፊት በርካታ አጨቃጫቂ ጉዳዮች ይቀርቡበት የነበረው የመገናኛ በዙሃን ምክር ቤት ከምሥረታው በኋላም ቢሆን ሁሉንም ጋዜጠኞችና የመገናኛ ብዙሀን ድርጅቶችን ይሁንታ ያገኘ አይመስልም። ገለልተኛ የሆኑም ሆነ አፍቃሬ መንግሥት የሆኑ አንዳንድ የመገናኛ ብዙሀን ከምክር ቤቱ አባልነት ራሳቸውን አግልለዋል።

ቀደም ባሉ ጊዜያት ምክር ቤቱን ለመመሥረት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ጋዜጠኞችም በጥርጣሬ ይመለከቱታል። ለጋዜጠኞች የሚሟገቱ እንደ ሲፒጄ ያሉ ድርጅቶችም ምሥረታዉን በርቀት እየተከታተሉት እንደሆነ ተነግሯል። ከዋሽንግተንዲሲ ወኪላችን ዝርዝሩን ልኮልናል።

ናትናኤል ወልዴ

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ