የሊብያዉ መሪ በኢጣልያ ጉብኝት ሊጀምሩ አንድ ቀን ሲቀራቸው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ፡ የኢጣልያ መሪዎች ሊብያ የሰብዓዊ መብቶችን እንድታከብር ተጽዕኖ እንዲያሳርፉ አሳስቦዋል። ከዚህ በተጨማሪም ወደ አውሮጳ በህገ ወጥ መንገድ በትናንሾቹ ጀልባዎች ሊገቡ የሚሞክሩ አፍሪቃውያን ስደተኞችን በግዳጅ ወደ ሊብያ ለመመለስ ሁለቱ ሀገሮች ቀደም ሲል የደረሱትን ስምምነት ወቅሶዋል። ሀና ደምሴ
HD/AA/SL