1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አማጽያን ትሪፑሊን በከፊል ተቆጣጠሩ

እሑድ፣ ነሐሴ 15 2003

የሊቢያ አማጽያን የኮነሪል ሞአመር ጋዳፊን መንግስት ለመገርሰስ የጀመሩትን ትግላቸዉን በማጠናከር ዋና መዲናይቱ ትሪፑሊን በከፊል መቆጣጠራቸዉን አስታወቁ።

https://p.dw.com/p/RhAa
ምስል dapd

ትናንት ለዛሪ አጥብያ በትሪፑሊ የሞአመር ጋዳፊ ወታደሮች የሚገኙበት ቦታ ከባድ ፍንዳታ መድረሱም ተመልክቶአል። ጦርነቱ ተባብሶ በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ የቴሌቭዥን ስርጭት ኮነሪል ሞአመር ጋዳፊ ደጋፊዎቻቸዉ ለወራት የዘለቀዉን ትግላቸዉን እንዲያቆሙ ጠይቀዋል። እንደ ጀርመኑ የመገናኛ ብዙሃን DPA ዘገባ የሊቢያዉ መሪ ኮነሪል ሞአመር ጋዳፊ ሊቢያን ለቀዉ ሽሽት ላይ ሳይሆኑ አልቀረም።

አዜብ ታደሰ
ልደት አበበ