አለመረጋጋት በጎንደር
ዓርብ፣ ሐምሌ 29 2008ማስታወቂያ
የግጭቱን መንስኤ የተከታተሉ የአይን ምስክር ደግሞ፤ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ ኮሚቴ አባል የሆኑት እና በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር የሚገኙት ኮሎኔል ደመቀ ዘዉዱ ዛሬ ጎንደር ፍርድ ቤት ይቀርባሉ የሚል መረጃ ያገኘዉ ሕዝብ ወደ ፍርድ ቤት በመሄድ የፍርዱን ሒደት ሲጠብቅ የገመተዉን በማጣቱ ሰላማዊዉ ሁኔታ ወደብጥብጥ መሻገሩን ገልጸዋል። እሳቸዉ እንደሚሉት የፀጥታ ኃይሎች ሕዝቡን ከአካባቢዉ ለመበተን በመጀመሪያ አስለቃሽ ጭስ ቀጥሎም ጥይት ተኩሰዋል። ስለሁኔታዉ የአማራ ክልላዊ መንግሥት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ንጉሡ ጥላሁንን ማብራሪያ እንዲሰጡን በስልክ ጠይቀናል። በትክክል ምን ተፈጠረ ለሚለዉ ጥያቄ መልስ በመስጠት ይጀምራሉ።
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ