ኃይሌ ገብረ-ሥላሴና የበርሊኑ ማራቶን፣8 መስከረም 2002ዓርብ፣ መስከረም 8 2002ከነገ በስቲያ በሚካሄደው ዓመታዊው የበርሊን ዓለም አቀፍ የማራቶን ሩጫ ውድድር፣ በዚህ ርቀት የዓለምን ክብረ-ወሰን የያዘው ዝነኛው አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ፣ ከጠንካራ ተፎካካሪዎች ይልቅ ይበልጥ የሚያሳስበው የአየር ጠባይ መሆኑን ጠቁሞአል።https://p.dw.com/p/JkC4ዝነኛው አትሌት ኃይሌ ገሥላሴ፣ እ ጎ አ መስከረም 28 ቀን 2008 ዓ ም፣ ከሌላዋ የማራቶን አሸናፊ ፣ ጀርመናዊቷ አትሌት፣ ኢሪና ሚኪቴንኮ ጋር፣ምስል APማስታወቂያ በጉጉት በሚጠበቀው ከአንድ መቶ ሺ በላይ አትሌቶች በሚሳተፉበት የበርሊኑ ማራቶን ውድድር፣ ጎዳና ላይ ወጥቶ የሚመለከተውና የሚያበረታታው ተመልካችም አኀዝ ከ አንድ ሚሊዮን እንደማያንስ ነው የሚገመተው። ከተመልካቾቹም መካከል ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን አይታጡም ። ይልማ ኃይለ ሚካኤል፣ ሒሩት መለሰ፣ ተክሌ የኋላ፣