1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ቻይና፤ በ5000 ሜትርና ማራቶን የሴቶች ሩጫ ኢትዮጵያ አሸነፈች

እሑድ፣ ነሐሴ 24 2007

ኢትዮጵያውያት አትሌቶች ቤጂንግ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች የአምስት ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር እሁድ ነሐሴ 24 ቀን፣ 2007 ዓ.ም. ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ተከታትለው በመግባት ድል አስመዘገቡ።

https://p.dw.com/p/1GOEw
China Leichtathletik WM in Peking Akmaz Ayana besondere WM-Momente
ምስል Reuters/L. Nicholson

አትሌት አልማዝ አያና ተፎካካሪዎቿን በረዥም ርቀት በመቅደም 14 ደቂቃ ከ26 ሰከንድ በሆነ ሰዓት ሩጫውን በአንደኝነት አጠናቃለች። ኹለተኛ ሰንበረ ተፈሪ፣ ሦስተኛ ደግሞ ገንዘቤ ዲባባ በመግባት የውድድሩ አሸናፊዎች ሆነዋል። ኢትዮጵያ ዛሬ ከዚህ ሩጫ በፊትም ሌላ አስደሳች ድል ተቀዳጅታለች።

በሴቶች የማራቶን ውድድር ማሬ ዲባባ አንደኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ 2ተኛውን ወርቅ አስመዝግባ ነበር። ላለፉት 9 ቀናት ቤጂንግ ውስጥ በተካሄደው እና ዛሬ የፍፃሜ ቀን በሆነው የአትሌቲክስ የዓለም ሻምፒዎና የሜዳሊያ የውጤት ሸንጠረዥ፤ 1ኛ ኬንያ 2ኛ ጃማይካ 3ኛ ዩናይትድ ስቴትስ፤ እንዲሁም ብሪታንያ 4ኛ ሲወጡ፤ ኢትዮጵያ በጠቅላላው 8 ሜዳሊያ በማግኘት 5ኛው ተርታ ላይ ተሰልፋለች። ጀርመን እንደ ኢትዮጵያ ስምንት ሜዳሊያ ኾኖም በኢትዮጵያ በአንድ ወርቅ ተበልጣ 7ኛ ደረጃን አግኝታለች።

ልደት አበበ

ማንተጋፍቶት ስለሺ