1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ቱርክ የኤርዶኻን መንግሥትና የገጠመዉ ተቃዉሞ

ሰኞ፣ ሰኔ 3 2005

ያም ሆኖ ጋዛፊን፥ሙባረክን፥ ሳሌሕን፥ ወይም አሰድን አይደሉም።ሥልጣን የያዙት በሕዝብ ተመርጠዉ እንጂ እንደ ቃዛፊ በመፈንቅለ መንግሥት፥ እንደ ዓሊ አብደላ ሳሌሕ በሞተ-ከዳ፥ እንደ ሙባረክ፥ እንደ አሰድ በዉርስ አይደለም።እርግጥ ነዉ እንደ አሰድ የጦር መኮንን ልጅ ናቸዉ

https://p.dw.com/p/18nGW
Turkish protesters, mostly soccer fans of Besiktas who call themselves "Carsi" celebrate in the rain at the city's Kugulu Park in Ankara, Turkey, Saturday, June 8, 2013. Turkey's Prime Minister Recep Tayyip Erdogan convened his party leadership Saturday as anti-government protests enter their ninth day, with thousands of people still occupying Istanbul's central Taksim Square and the main Kizilay Square in Ankara. (AP Photo / Burhan Ozbilici)
ተቃዉሞ-ኢስታንቡልምስል picture-alliance/AP

ጥር አጋማሽ-ሁለት ሺ አስራ-አንድ።ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ።ካይሮ ተሕሪር አደባባይ ሞላ-ጠርቃ፥ ሞቅ ደግሞም ወበቅ ማለት ያዘች።

ኢስታንቡል-ታክሲም አደባባይ በቀደም።

ይራራቃሉ።በሁለት ዓመት ከመንፈቅ እድሜ ይበላለጣሉም። ግን ይመሳሰላሉ።አንድ ይሆኑ ይሆን? የአንካራ መሪዎችን አመራር እንዴትነት፣የኢስታንቡሉን ተቃዉሞ ሰበብ ምክያት እየጠቃቀስን ላፍታ አብረን እንጠይቅ።


የሃያ-ስድስት ዓመቱ ቱኒዚያዊ ወጣት መሐመድ ቡዋዚዚ ታሕሳስ 2010 አካሉ ላይ የቸለሰዉ ቤንዚን እና የለከሰዉ ክብሪት የሱን ሕይወት ቀጥፎ የቱኒዚያዎችን ቁጣ ሲያቀጣጥል እንደ አብዛኛዉ ዓለም የፓሪሶችን አፀፋ ከሩቅ አድፍጦ ከማየት በስተቀር ብዙ ያሉ-ያደረጉት አልነበረም። ከቡዋዚዚዋ ከተማ ሳይዲ ቡዚድ ላይ የገነፈለዉ ሕዝባዊ ቁጣ ቱኒዚያን አዳርሶ የቱኒዙን ጠንካራ መሪ የዘይን ኤል አቢዲን ቤን ዓሊን ሥርዓት በገረሠሠ ማግሥት ወደ ካይሮ ሲሸጋገር ግን በጥሞና ይከታተሉት ነበር።ካይሮ፥-


ከተሕሪር አደባባይ ጩኸቱ ሲቀልጥ የያኔዉ የሐገሪቱ ፈርጣማ መሪ ሆስኒ ሙባረክ የሕዝባቸዉን ጥሪ ከልብ እንዲሰሙ እንደ ወዳጅ ቀድመዉ ከመከሩ፥ እንደ ሕዝብ ጥያቄ አክባሪ ደፍረዉ ካሳሰቡ ጥቂት መሪዎች አንዱ ነበሩ።ጠቅላይ ሚንስትር ሬሴፕ ተይፕ ኤርዶኻን።ትናንት በርግጥ ዛሬ አይደለም።ኤርዶኸንም በምንም መመዘኛ ሙባረክን አይመስሉም።ኢስታንቡሎች ግን በሁለት ዓመት ከመንፈቃቸዉ ካይሮዎችን ባይሆኑ መስለዋል።እንዲሕ ይሉ ገቡ።ሴትዮዋ፥-

«እዚሕ የተገኘነዉ ሕዝቡን ለመደገፍ ነዉ።በነፃ የማሰብና የመናገር መብታችንን ለመጠየቅ እራሳችንን ለመግለጥ።» ሰዉዬዉም፥-አከሉበት፥-«የዚሕ ሁሉ ተቃዉሞና መልዕክት ሲታይ ኤርዶሐን ከእንግዲሕ ቦታ የላቸዉም»

የቱኒዝ ካይሮዉ አስተምሕሮት የነቀነቀዉ የየመን ሕዝብ የሰነዓን አደባባዮች ሲያደበላልቅ ሪያድ፥ ዶሐ፥ ዋሽግተኖችኖች የሚሉ የሚደርጉትን ከመከታተል ባለፍ ያሉ ያደረጉት ከነበረ ብዙም አልተሰማም።የኮሎኔል ሙዓመር ቃዛፊን ሥርዓት፣ የእሳቸዉን፣ የልጆቻቸዉንና የብዙ ሺሕ ሊቢያዉያንን ሕይወት ላጠፋዉ ዘመቻ ኒኮላይ ሳርኮዚ ምዕራቡን ዓለም ሲመሩና ሲያስተባብሩ፣ ሙስሊሙን ዓለም፣ከመሩት ሰወስት መሪዎች አንዱ ግን እሳቸዉ ነበሩ።ሁለቱ ሐማድ ቢን ኸሊፋ አ-ሳኒ እና አብዱላሕ ኢብን አብድል አዚዝ።

በሽር አል አሰድን እንደ ቃዛፊ ለመፈጠም ያለመዉ የምዕራባዉያንና የተከታዮቻቸዉ ዘመቻ ጠቅላይ መሪ በርግጥ ባራክ ኦባማ ናቸዉ።የሶሪያ ሸማቂዎችን ያስጠጉት፥ የሚያደራጁ የሚስታጠቁት ደፋር ፊት አዉራሪ ግን እሳቸዉ ናቸዉ።ኤርዶኸን።

ኢስታንቡል ቤንጋዚ ወይም ሆምስ አይደለችም።ኢስታንቡሎች እንደ ቤንጋዚ ሆምሶች ጠመንጃ መንከስ አያስፈልጋቸዉምም።እንዲያዉ ምናልባት ነገሮች ተቀያይረዉ ቢፈልጉ እንኳን በኩርዶች የደረሰና የሚደርሰዉን ማየት፥ ማስተዋል አለባቸዉ።ከሁሉም በላይ ኤርዶኻን እንደ ቃዛፊ ወይም እንደ አሰድ የዋሽግተን ብራስልሶችን ጥቅምና ትዕዛዝ እስኪጥሱ መጠበቅ ግዳቸዉ ነዉ። ሰዉዬዉ የሚያደርጉት አይመስልም።

ብቻ ምን ይታወቃል። ኮሎኔል ሙዓመር ቃዛፊ በዋሽግተን፥-ለንደን-ፓሪስ፥ በሪያድ፥ ዶሐ፥ አንካራዎች ድጋፍ የተደራጁ፥ የሰለጠኑና የታጠቁ ተቃዋሚዎቻቸዉ ቤንጋዚ ላይ ምሽግ መማስ፥ ጠመንጃ መተኮስ ሲጀምሩ «አሸባሪ አይጦች» ብለዋቸዉ ነበር።

በሪያድ ዶሐዎች ገንዘብ፥ በዋሽግተን ብራስልሶች ሥለላ፥ ዲፕሎማሲ እየተረዱ አንካራዎች በፈቀዱት ምድር መሽገዉ የሶሪያ መንግሥትን የሚወጉት አማፂያን ለፕሬዝዳት በሽር አል-አሰድ «የተደራጁ አሸባሪዎች» ናቸዉ።ተሕሪር አደባባይ የፕሬዝዳት ሆስኒ ሙባረክን አገዛዝ በሚቃወመዉ ሕዝብ መጥለቅለቅ በጀመረበት ሰሞን ሙባራክ ግመል ጋላቢ፥ ጩቤ ታጣቂ ነዉጠኛ ደጋፊዎቻቸዉን እዚያዉ አደባባይ አፍስሰዋቸዉ ነበር።

ያኔ ሙባረክ ደጋፊዎቻቸዉን ከተቃዋሚዎቻቸዉ ማጋጨት፥ የአብዛኛዉን ሕዝብ ጥያቄን አልቀበልም ማለታቸዉን የተቹት ኤርዶኻን ትናንት አንካራ ላይ ደጋፊያቸዉን አሰለፉ።ያኔ የቃዛፊ አሸባሪ አይጦችን እንደ ነፃነት ተዋጊ የረዱ የደገፉት፥ አሁን የአሰድን «የተደራጁ አሸባሪዎች» የሚያደራጁት ኤርዶኻን ተቃዋሚዎቻቸዉ በዚያዉ ቃል አወገዟቸዉ።አሸባሪ።

«ሥርዓተ-አልበኞች እና አሸባሪዎች የሕዝብ አደባባይን እንዲቆጣጠሩ መፍቀድ አለብን-እንዴ? ምን ለማግኘት ነዉ የሚታገሉት።ፖሊስ የሚፋለመዉ ይሕን ሁኔታ ለመከላከል ነዉ።እፍኝ የማይሞሉ ወርሮ በሎች ያደረጉትን ማድረግ አንፈልግም።የሰላማዊ ሰዎችን መኪኖች ሰባብረዋል።የዚችን ሐገር ጠቅላይ ሚንስትር እስከመስደብ የደረሱ ወራዶች ናቸዉ።»


ያም ሆኖ ጋዛፊን፥ሙባረክን፥ ሳሌሕን፥ ወይም አሰድን አይደሉም።ሥልጣን የያዙት በሕዝብ ተመርጠዉ እንጂ እንደ ቃዛፊ በመፈንቅለ መንግሥት፥ እንደ ዓሊ አብደላ ሳሌሕ በሞተ-ከዳ፥ እንደ ሙባረክ፥ እንደ አሰድ በዉርስ አይደለም።እርግጥ ነዉ እንደ አሰድ የጦር መኮንን ልጅ ናቸዉ።

ከወታደር አባታቸዉ ድፍረትን፥ የትምሕርትን ጥቅም፥ ሐይማኖትን ጠንከር አድርጎ የመያዝን አስፈላጊነት፥ ደሐን የመርዳት፥ ሐገርን የመዉደድ ፍቅርን እንጂ በመፈንቅለ መንግሥት የተያዘ ሥልጣንን አልወረሱም።ገና በወጣትነታቸዉ ፖለቲካንና ስፖርትን እኩል ይወዱ ነበር።የፖለቲካ ጥልፍልፍን አንድ ሁለት ያሉትም፥ የተለማመዱትም ገና የዩኒቨርስቲ ተማሪ እያሉ የተማሪዎች ማሕበር አባል ሆነዉ እንጂ እንደ ሌሎቹ ሥልጣን ከያዙ በኋላ አልመዱትም ወይም ድንገት አልተሞጀሩበትም።

በ1954 በጥንታዊቷ፥ በታሪካዊቷ ትልቅ የንግድ ከተማ ተወለዱ።ኢስታንቡል።በ1980 የዩኒቨርስቲ ተማሪ እያሉ የቱርክ ጦር ሐይል የያኔዉን የቱርክ ሲቢላዊ አስተዳደር ከስልጣን አስወግዶ ሥልጣን መያዙን ከጓደኞቻቸዉ ጋር ሆነዉ አጥብቀዉ ተቃዉመዉት ነበር።ያኔ ሐያ ስድስት ዓመታቸዉ ነበር።ዘንድሮ የያኔ-እድሜያቸዉን የያዙ ወጣቶች ሲቃወሟቸዉ ግን አወገዙ፥ ረገሟቸዉም።

«የራሳቸዉን ጠቅላይ ሚንስትር የሚያወግዙ ወጣቶች የኔ ወጣቶች ሊሆኑ አይችሉም።የቤቶች መስኮቶችን የሚሰባብሩ ወጣቶች መብታቸዉን በትክክል የሚጠቀሙ ወጣቶችን መልክና ባሕሪ ሊይዙ አይችሉም።ሱቆችን የሚያፈራሱ በዚች ሐገር ያላቸዉን መብት በተገቢዉ መንገድ ለመጠቀም የሚሹ ናቸዉ ሊባሉ አይቻልም።»

ከ1980 ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ እስልምናን የሚያጠብቀዉ ፓርቲ አባል ነበሩ።በ1994 በተደረገዉ የከተሞች ምርጫ የተወለዱባትን ትልቅ ከተማ የኢስታንቡል የከንቲባነት ሥልጣን ሲይዙ ጠንካራ ሐይማኖታዊ መርሕ ይከተሉ ይሆናል ተብለዉ በተቃዋሚዎቻቸዉ ዘንድ ሲተቹ ነበር።አንዳድ ሥፍራ አልኮሖን እንዳይሸጥ ከልክለዋል።ከዚሕ ይልቅ ግን የተዘበራረቀችዉን ግዙፍ ከተማ ዘመኑ-የሚጠይቀዉን የከተማ ማዕረግ አጎናፀፏት።

አራት ዓመት ብቻ በዘለቀ-ሥልጣናቸዉ ኢስታንቡል ላይ የተንሰራፋዉን ሙስናን ነቅለዉ ጣሉ።ብዙ መቶ ኪሎ ሜትር የሚረዝም ቧንቧ ዘርግተዉ የዉሐ ችግሯን አስወገዱ።ከሐምሳ በላይ ድልድዮች፥ ብሺ ኪሎ ሜትር የሚረዝሙ መንገዶች ገንብተዉ የትራፊክ መጨናነቅን አስወገዱ።የአየር ብክለትን በሰባ-አራት ከመቶ ቀነሱ።ዘመነ-ሥልጣናቸዉ ሲያበቃ ከተማይቱ የነበረባትን ሁለት ቢሊዮን ዶላር ዕዳ ከፍለዉ ለኢስታንቡል አራት ቢሊዮን ዶላር ከኢስታንቡል ባንክ አስቀምጠዉ በ1998ተሰናበቱ።

ዛሬ የዓለም የከንቲቦች ጉባኤ የሚባለዉን ማሕበር የመሠረቱት እሳቸዉ ናቸዉ።ኤርዶኸን።ለዚሕም ሐቢታት የተሰኘዉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሽልማትን ተሸልመዋል። ሥልጣን በለቀቁ ባመቱ ግን መጥፎ ግጥም ሕዝብ ፊት አንብበሐል ተብለዉ የፓርቲ ሥልጣናቸዉን ተገፈዉ አስር ወር እስራት ተፈረደባቸዉ።አራት ወር ታስረዉ ሲፈቱ የፍትሕ እና የልማት ፓርቲ (AKP በቱርክኛ) የተሰኘዉን የፖለቲካ ማሕበር መሥርተዉ አንካራ ቤተ-መንግሥት የሚገቡበትን ሥልት ያዉጠነጥኑ ያዙ።

አልቆዩም በሁለት ሺሕ ሁለት በተደረገዉ ምርጫ አሸንፈዉ ካሰቡት ደረሱ።ሐያ-አምስተኛዉ የቱርክ ጠቅላይ ሚንስትር።በተከታታይ ለሰወስት ዘመነ-ሥልጣን ቱርክን ሲመሩ የሐገሪቱን ምጣኔ ሐብት አንቻረዉታል። ቱርክ የአዉሮጳ ሕብረት አባል ለመሆን ከሕብረቱ ጋር የተፈራረመችዉ ሕብረቱ እንደተመሠረተ ነበር።ዉሉ ከተፈረመ-ከአርባ አምስት ዓመት በኋላ አባል የመሆኑን ድርድር የጀመሩት ግን ኤርዶኻን ናቸዉ።

የአዉሮጳ ሕብረት አባል የሆኑት ግሪኮች፥ ስጳኞች፥ ፖርቱጋሎች፥ ኢጣሊያዎች፥ አየር ላንዶች ሲሽመደመዱ የኤርዶኻንዋ ቱርክ ኢኮኖሚ በየዓመቱ የሰባት ነጥብ ሰወስት በመቶ ግስጋሴዉ እንደቀጠለ ነዉ።ሥልጣን ሲይዙ ቱርክ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት IMF 23.5 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ ነበረባት።ኤርዶኻን አብዛኛዉን ዕዳ ከፍለዉ ባለፈዉ ዓመት ማብቂያ የቀረባት ዘጠኝ መቶ ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነዉ።ዘንድሮ ተከፍሎ ያልቃል-ነዉ የኤርዶኻን ዕቅድ።

ኩርዶች በብዛት በሚኖሩበት አካባቢ ትምሕርት በኩርዶች ቋንቋ እንዲሰጥ፥ ጋዜጦች እንዲታተሙ ፈቅደዋል።ከማርኪስስቱ ከኩርድ ነፃ አዉጪ ፓርቲ (PKK) የሰላም ሥምምነት ተፈራርመዋል።

ኤርዶሐን ከቅርብ አመታት ወዲሕ በሚተቿቸዉ ጋዜጠኞችና በመብት ተሟጋቾች ላይ የሚወስዱት ጠንካራ እርምጃ ግን ሁሉም ሲሳካላቸዉ ሁሉም ባልኩት ይደር ስሜት የታበዩ አስመስሎባቸዋል። በሁለት ሺሕ ሰወስት ሥልጣን እንደያዙ ከሁሉም ጎረቤቶች ጋር «የዜሮ-ችግር» የወዳጅነት መርሕ እንከተላለን ብለዉ ነበር።የሊባኖስ ፖለቲከኞችን ለማስማማት የተደረገዉን ጥረት ደግፈዉ ነበር።እስራኤልና ሶሪያን ለማደራደር ብዙ ሞክረዉም ነበር።ዛሬ ግን በማደራደር ሰበብ ብዙ ሚስጥር ያጋሯቸዉን አሰድን ቀንደኛ ጠላታቸዉ አድርገዋቸዋል።

ከዉጪም ከዉስጥም የተጠራቀመዉ ቅሬታ ለተቃዋሚዎቻቸዉ ጉልበት ነዉ-የሆነዉ።እንጂ መንግሥታቸዉ አንድ አደባባይ አፍርሶ አንድ የገበያ አዳራሽ ለማስገንባት ማቀዱ ይሕን ያሕል የሕዝብ ቁጣና ተቃዉሞ ይቀሰቅሳል ማለት በርግጥ ሰበብ እንጂ ምክንያት ነዉ-ማለት ይከብደል።ብቻ ናፋቂዉ አፈፃፀሙና ፍፃሜዉ ነዉ።

ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ


























Protesters run on June 9, 2013 from tear gas and water cannons used by Turkish police to disperse a demonstration on Kizilay square in Ankara. Turkish Prime Minister Recep Tayyip Erdogan on June 9 told supporters his patience "has a limit" as he went on the offensive against mass protests to his Islamic-rooted government's decade-long rule. As tens of thousands of protesters massed in Istanbul, Ankara and the western city of Izmir, in unrest now in its 10th day, Erdogan staged his own rallies across three cities to fire up loyalists of his ruling Justice and Development Party (AKP). The nationwide unrest first erupted on May 31 with a tough police crackdown on a campaign to save Istanbul's Gezi Park from demolition. The trouble spiralled into mass protests against Erdogan and his party, seen as increasingly authoritarian. AFP PHOTO / MARCO LONGARI (Photo credit should read MARCO LONGARI/AFP/Getty Images)
ግጭትምስል Marco Longari/AFP/Getty Images
Anti-government protesters shout slogans and wave Turkey's national flags during a demonstration in central Ankara June 6, 2013. Erdogan denounced those behind a week of violent demonstrations on Thursday, causing a sell-off on the Turkish stock exchange from investors worried that his defiant rhetoric will further enflame public wrath. Speaking during a visit to Tunisia, Erdogan vowed to press ahead with plans for construction in an Istanbul park which triggered the unrest across the country. Three people have been killed and more than 4,000 injured in demonstrations that have seen police fire tear gas at angry crowds. REUTERS/Umit Bektas (TURKEY - Tags: POLITICS CIVIL UNREST)--eingestellt von haz
ምስል Reuters
Riot police lean on their shields during a stand off with protesters in Ankara, Turkey, Sunday, June 9, 2013. In a series of increasingly belligerent speeches to cheering supporters Sunday, Turkey's prime minister Recep Tayyip Erdogan launched a verbal attack on the tens of thousands of anti-government protesters who flooded the streets for a 10th day, accusing them of creating an environment of terror.(AP Photo/Vadim Ghirda)
ፀጥታ አስከባሪዎችምስል picture-alliance/AP
Anti-government protesters shout slogans during a demonstration in central Ankara June 8, 2013. Turkish Prime Minister Tayyip Erdogan's AK Party on Saturday ruled out early elections as thousands of anti-government demonstrators defied his call for an immediate end to protests. REUTERS/Umit Bektas (TURKEY - Tags: POLITICS CIVIL UNREST)
ተቃዉሞ-አንካራምስል Reuters
Bildnummer: 59790514 Datum: 07.06.2013 Copyright: imago/Xinhua (130607) -- ISTANBUL, June 7, 2013 (Xinhua) -- Turkish Prime Minister Recep Tayyip Erdogan speaks during the conference in Istanbul on June 7, 2013. Istanbul Conference of the Ministry for EU affairs was held on Friday. Topics on Global economic challenges and prospects, reconciling democracy and security in the age of globalization, shaping Turkey-EU relations in global governance were discussed during the meeting. (Xinhua/Lu Zhe) (dtf) TURKEY-ISTANBUL-EU AFFAIRS-CONFERENCE PUBLICATIONxNOTxINxCHN People Politik premiumd xbs x0x 2013 quer 59790514 Date 07 06 2013 Copyright Imago XINHUA Istanbul June 7 2013 XINHUA Turkish Prime Ministers Recep Tayyip Erdogan Speaks during The Conference in Istanbul ON June 7 2013 Istanbul Conference of The Ministry for EU Affairs what Hero ON Friday ON Global Economic Challenges and Prospects Democracy and Security in The Age of Globalization Shaping Turkey EU relations in Global Governance Were discussed during The Meeting XINHUA Lu Zhe Turkey Istanbul EU Affairs Conference PUBLICATIONxNOTxINxCHN Celebrities politics premiumd xbs x0x 2013 horizontal
ኤርዶኻንምስል imago/Xinhua