ተከሳሹ አጭበርባሪ ካገር ወጣ
ሐሙስ፣ መስከረም 15 2007ማስታወቂያ
ሠዎችን ወደ አዉሮጳና አሜሪካ እልካችኋላሁ በማለት በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ብር ያጋበሰ አንድ ኢትዮጵያዊ ከሐገር መዉጣቱ ተነገረ።ሳሙኤል ቦጋለ የተባለዉ ግለሠብ ወደ ዉጪ እልካችኋላሁ በማለት ከበርካታ ሰዎች ከሃያ ሚሊዮን ብር በላይ መዝረፉን ተበዳዮች አስታዉቀዋል።ተበዳዮቹ እንደሚሉት ተጠርጣሪዉ ክስ ተመሥርቶበት ከሐገር እንዳይወጣ በፍርድ ቤት ቢታገድም በኬንያ አቋርጦ ዱባይ መግባት አልተሳነዉም።የኢትዮጵያ ፀጥታ አስከባሪዎች «ወንጀለኛ» የሚሏቸዉን ሰዎች ዉጪ ሐገር ድረስ እየዘመቱ ሲይዙ የፍርድ ቤት ብይንን ያላስከበሩበት ምክንያት እያነጋገረ ነዉ።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ