ተቃውሞ በኢትዮጵያ ቆንስላ ላይ
ዓርብ፣ መጋቢት 28 2004ማስታወቂያ
በሊባኖስ ቤይሩት ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ፣ ህይወቷን አጠፋች የተባለችው የዓለም ደቻሳ ሞት ከተነገረበት ማግስት አንስቶ ቤይሩት ወደሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ በመሄድ ቁጣቸውን ሲያሰሙ መቆየታቸውን የጂዳው ወኪላችን ነበዩ ሲራክ ዘግቧል ። ዓለም ቆንስላው በር ላይ ስተሰቃይ በነበረበት ወቅት የሚደርስላት ማጣቷ ያስቆጫቸው እነዚሁ ኢትዮጵያውያን የቆንስላው ባለሥልጣናት መብታችንን ያስጠብቁ አለያም ለቀው ይውጡ በማለት በተለያዩ መንገዶች ተቃወሞአቸውን እየገለጹ ነው ። በቤይሩት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጀነራል በበኩላቸው ዜጎች ህጋዊ ከለላ እንዲያገኙ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና ጉዳዩንም የሊባኖስ መንግሥት እየተመለከተው መሆኑን ለዶቼቬለ አስታውቀዋል ።
ነብዩ ሲራክ
ሂሩት መለሥ
ሸዋዬ ለገሠ