1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ተቃውሞና የወጣቶች ተሳትፎ በኢትዮጵያ

ዓርብ፣ ነሐሴ 6 2008

በዛሬው የወጣቶች መሰናዶ እሸቴ በቀለ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተቀሰቀሱ ተቃውሞዎች ላይ አተኩሯል። በመሰናዶው ጦማሪው በፍቃዱ ኃይሉ እና የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ ሊቀመንበር ወጣት ነጂባ አክመልን አነጋግሯል።

https://p.dw.com/p/1JhKD
Äthiopien Protest
ምስል Reuters/T. Negeri

ተቃውሞና የወጣቶች ተሳትፎ በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተቀሰቀሰው ተቃውሞ በማህበራዊ-ድረ ገጾች የሚደረጉ ውይይቶችን ተቆጣጥሯል። በአብዛኛው ወጣቶች የሚበዙበት የማህበራዊ ድረ-ገጾች ለወቅታዊው የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ከሌሎች የመገናኛ ብዙኋን ተመራጭ የሆኑ ይመስላል። በውይይቶቹ እና ክርክሮቹ የጸጥታ ኃይሎች በተቃዋሚዎች ላይ የወሰዱትን እርምጃ የሚያወግዙ አስተያየቶች ይበዛሉ። የዛኑ ያክል ተቃውሞዎቹን የሚያወግዙም አልጠፉም።

የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ ሊቀመንበር ወጣት ነጂባ አክመል በተለያዩ አካባቢዎች በተቀሰቀሱ ተቃውሞቆች የተሳተፉ ወጣቶች ጥቂት ናቸው የሚል እምነት አላቸው።

ፀሃፊው፤የሰብዓዊ መብት አራማጁ እና ጦማሪው በፍቃዱ ኃይሉ አሁን የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታን ከሚከታተሉ አንዱ ነው።

በፍቃዱ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በሚታየው የአደባባይ ተቃውሞ የማህበራዊ ድረ-ገጾች ከፍ ያለ ሚና መጫወታቸውን ይናገራል።

እሸቴ በቀለ

ሒሩት መለሰ