1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ብሪታኒያና አዲሱ የስደተኞች ህግ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 21 2007

በእንግሊዝና በዌልስ ግዛቶች ሥራ ላይ ይውላል ተብሎ በሚጠበቀው በአዲሱ ህግ ፣ህገ-ወጥ የሚባሉ የውጭ ዜጎች ከተያዙ የስድስት ወር እሥራት እንደሚጠብቃቸውና እሥራታቸውንም እንደጨረሱ ወደ መጡበት ሃገር እንደሚባረሩ ተገልጿል ።

https://p.dw.com/p/1GMuN
Frankreich Flüchtlinge Eurotunnel Calais
ምስል Getty Images/AFP/P. Huguen


የብሪታኒያ መንግሥት በሃገሪቱ በህገ ወጥ መንገድ የሚኖሩና ያለ ፈቃድ የሚሰሩ የውጭ ዜጎችን ማሰርና ከብሪታኒያ እንዲባረሩ ማድረግ የሚያስችል አዲስ ህግ ሥራ ላይ እንደሚውል ማሳወቁ እያነጋገረ ነው ። መንግሥት ህጉን የሚያወጣው ወደ ብሪታኒያ በህገ ወጥ መንገድ የሚሰደደው ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ መሆኑን ይናገራል ። የመብት ተሟጋቾች በበኩላቸው መንግሥት የሚያቀርበው ምክንያት ተቀባይነት የለውም ሲሉ ይሟገታሉ ። በእንግሊዝና በዌልስ ግዛቶች ሥራ ላይ ይውላል ተብሎ በሚጠበቀው በአዲሱ ህግ ፣ህገ-ወጥ የሚባሉ የውጭ ዜጎች ከተያዙ የ6 ወር እሥራት እንደሚጠብቃቸውና እሥራታቸውንም እንደጨረሱ ወደ መጡበት ሃገር እንደሚባረሩ ተገልጿል ። ህገ ወጥ የሚባሉትን የሚያሠሩና ቤት የሚያከራዩም ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ተነግሯል ።

ድልነሳ ጌታነህ

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ