በጀርመን አንድ የኒዎ ናዚዎች ቡድን ላይ የጀመረዉ ምርመራ
ሰኞ፣ ሚያዝያ 28 2005የዛሪ ሁለት ዓመት መንገድ ዳር የሆነ ነገር ተቃጥሎ አመድ ለብሶ የታየዉ መለስተኛ አዉቶቡስ ዉስጥ ፖሊስ የሁለት ወጣቶች ሪሳ በማግኘቱ ነበር ተጠርጣሪዎቹ፤ በድንገት የተገኙት እና የተያዙት ። ከጥቂት ሰአታት በፊት በዚያኑ ቀን በአካባቢዉ በሚገኝ አንድ ባንክ 70 ሺ ይሮ ሲዘረፍ ሁለት የብስክሌት አሽከርካሪዎች እንደነበሩ የአይን ምስክሮች ገልጸዋል።
እጅግ አክራሪ የሆነው በህቡዕ ይንቀሳቀስ የነበረው የአፍላ ናዚዎች እንቅሥቃሴ፤ በተለያዩ ጊዜያት 9 ቱርካውያንናና አንድ ግሪካዊ እንዲሁም አንዲት ጀርመናዊት ፖሊስ መግደሉ ታውቋል። ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረበችው ዋና ተከሳሽ፤ ፤ የዚህ ሁሉ ግድያ ዋና ግብረ- አበር ተብላ የተጠረጠረችው ቤአተ ቼፐ የተባለችው ናት። ዑቨ ሙንድሎስና ዑቨ Böhnhardt የተባሉት የዚህ የህቡዕ ድርጅት መሥራቾች፤ እንደተነቃባቸው ህይወታቸውን በራሳቸው እጅ ማጥፋታቸው ነው የተነገረው። ዋናው ጥያቄ እነዚህ ወገኖች የመንግሥት ፀጥታ አስከባሪ ኃይሎች ሳያውቁባቸው እንዴት 10 ዓመት ሙሉ አቅድ እያወጡ የሰው ነፍስ አጠፉ ? የሚለው ነው። የፍርዱ ምርመራና ሂደት ሰፊ ዓለም አቀፍ ትኩረት አግኝቷል ፣ በተለይ በቱርክ!በዛ ያሉ የቱርክ የህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት አባላትም ፣ የምርመራውን ሂደት ለመከታተል ወደ ሙዑሸን ተጉዘዋል። ዝርዝሩን የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ሃይለሚካኤል አጠናቅሮታል።
ይልማ ሃይለሚካኤል
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ