1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በብሪታንያ የሚኖሩ ኤርትራዉያን አስተያየት 

ሰኞ፣ ሐምሌ 2 2010

የኢትዮጵያና የኤርትራ መሪዎች ከ ሃያ ዓመት በኋላ በሁለቱ ሃገሮች መካከል ሠላምን ለማምጣት እና መልካም ጉርብትናን ለማጠናከር መስማማታቸው በተለይ ለሁለቱ ሕዝቦች ታላቅ እፎይታ መሆኑን በውጭ በብሪታንያ የሚኖሩ ኤርትራውያን ገለጹ ።

https://p.dw.com/p/316Zn
UK geplante Wartungsarbeiten beim Big Ben
ምስል Getty Images/AFP/B. Stansall

የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ህዝብ በሃገራቱ ሰላም መስፈኑ አስመራ ላይ የተዉለበለበዉ የሰላም ዘንባባ ፤ እናቶች በእልልታ፤ ወጣቱ ሆታ፤ የሁለቱን ሃገሮች ሰንደቃላማ እያዉለበለበ እያዜመ የኢትዮጵያዉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በሞቀ ድግስ መቀበሉ ለሰላም እና ለፍቅር ያለዉን ፍላጎት በጉልህ ያሳየ ነዉ። በሁለቱ ሃገራ ይህ አይነት ሰላም መንገሱ የሁለቱን ሃገራት ብቻ ሳይሆን ለቀጠናዉ፤ ብቻ ሳይሆን በዓለም ያለዉን ሰላም ፈላጊ ማኅበረሰብ ያስፈነደቀ መሆኑን ኤርትራዉያኑ ገልፀዋል።  የለንደኑ ወኪላችን በለንደን ነዋሪ የሆኑ ኤርትራዉያንን ስለ ኢትዮ ኤርትራ አዲስ ግንኙነት አስተያየታቸውን ጠይቆ አጠር ያለ ጠገባ ልኮልናል። 


ድልነሳህ ጌታነህ
አዜብ ታደሰ 
ኂሩት መለሰ  

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ