በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ውይይት በብራስልስ
ቅዳሜ፣ መጋቢት 28 2011ማስታወቂያ
ዛሬ ቤልጄም ብራስልስ ውስጥ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል። የስብሰባው መሪ እና ስብሰባውን የጠራው « ድልድይ» ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ አበራ የማነዓብ ለ DW እንደተናገሩት የስብሰባው ዓላማ በሀገር ውስጥ ለአንድ ዓመት ያህል እየተካሄደ ያለው ለውጥን ለመገምገም እና ምን መደረግ እንዳለበት ለመመካከር ነው። በውይይቱ ላይ እንዲካፈሉ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች እና የሲቪል ማህበረሰብ መጠራታቸውንም ገልጸውልናል። ይህንን ስብሰባ ለመከታተል በቦታው የተገኘው ገበያው ንጉሴ ይህንን የውይይት መድረክ ያዘጋጀው ማን እንደሆነ እና በውይይቱ ላይ ስለተነሱት ሀሳቦች ገልፆልናል።
ገበያው ንጉሴ
ልደት አበበ