1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአፍሪቃ የጸጥታ ጉዳይ የጀርመን ሚና

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 11 2008

ጀርመን በአፍሪቃ የጸጥታ ጉዳዮች ከየሃገራቱ በተናጠል እና በአፍሪቃ ኅብረት ጥላ ሥር የበኩሏን እገዛ እያደረገች እንደሆነ ተገለጸ።

https://p.dw.com/p/1IYWJ
München Sicherheitskonferenz - Panel Discussion "Africa: Keeping P(e)ace"
ምስል MSC / Mueller

[No title]

ከአፍሪቃ፣ ከአዉሮጳ እና አሜሪካ የተዉጣጡ 60 ከፍተኛ ባለስልጣናት በተሳተፉበት ባለፈዉ ሳምንት አዲስ አበባ ላይ የተካሄደዉ የሙኒክ የጸጥታ ጉባኤ፤ ሽብር እና ጽንፈኝነትን ስለመዋጋት፣ በሰሜን እና ምሥራቅ አፍሪቃ ቀዉስን ስለመከላከልና ማስተዳደርን አስመልክቶ ተነጋግሯል። የአፍሪቃ ሃገራት የዉስጥ ሰላም ወሳኝ መሆኑ ያመለከተዉ ጉባኤ፤ በተለይ በምርጫ ሰሞን በየሃገራቱ የሚታየዉን አመፅና ዉዝግብም በችግርነት ነቅሶ ተወያይቶበታል። በሳምንቱ ማለቂያ ባህር ዳር ላይ በተካሄደዉ የጣና መድረክ ወይም ጣና ፎረም ላይ የተሳተፉት በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ዮአኺም ሽሚት ለዶቼ ቬለ እንደተናገሩት የአፍሪቃ የጸጥታ ችግር፤ የዓለም የጸጥታ ችግር በመሆኑ ጀርመን በምታደርገዉ ድጋፍ ትገፋበታለች። አምባሳደሩን ያነጋገራቸዉ ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ