1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአዲስ አበባ የታክሲዎች ከፊል የስራ ማቆም አድማ

ሰኞ፣ ግንቦት 8 2003

ዛሬ አዲስ አበባ በበርካታ አከባቢዎች ታክሲዎች ስራ አቁመው ውለዋል። አዲሱ የስምሪት መመሪያ ጥቂቶችን ለመጥቀም የወጣ ነው ሲሉ ባለታክሲዎቹ አማረዋል።

https://p.dw.com/p/RODK
ምስል picture alliance/dpa

የዛሬ ሳምንት ሰኞ የአዲስ አበባ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ፤ የአዲስ አበባ ታክሲዎችን ስምሪትና የዋጋ ተመን የሚያሳይ አዲስ መመሪያ አዋጣ። መመሪያው አርብ ዕለት ጀምሮ ተግባራዊ ሆነ። አርብ በተወሰነ ደረጃ ዛሬ ደግሞ ከፊል አዲስ አበባን የሸፈነ የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ ተደረገ። ዘጋቢያችን ታደሰ እንግዳው ያነጋገራቸው አንዳንድ የታክሲ አሽከርካሪዎች፤ ገንዘብ ተቀባዮችና ተራ አስከባሪዎች እንደሚሉት መመሪያው ጥቂቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የወጣ ነው። ዛሬ አዲስ አበባ በከፊል ጭር ብላ ነው የዋለችው። መንግስት የተፈጠረው ችግር ጊዜያዊ ነው። ዘላቂ መህትሄ እየፈለኩለት ነው ይላል።

ታደሰ እንግዳው

መሳይ መኮንን

ሂሩት መለሰ