1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በቴይለር ላይ የተላለፈው ብይን

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 18 2004

ዘሄግ ኔዘርላንድስ የተሰየመው የሴራልዮን ልዩ ፍርድ ቤት በቀድሞው የላይቤሪያ መሬ ቻርልስ ቴይለር ላይ ዛሬ የጥፋተኝነት ብይን አሳልፏል ። ፍርድ ቤቱ ቴይለር በተመሠረቱባቸው 11 የወንጀል ክሶች ጥፋተኛ መሆናቸውን አሰታወቋል ።ቴይለር

https://p.dw.com/p/14lcg
ምስል picture-alliance/dpa

ዘሄግ ኔዘርላንድስ የተሰየመው የሴራልዮን ልዩ ፍርድ ቤት  በቀድሞው የላይቤሪያ መሬ ቻርልስ ቴይለር ላይ ዛሬ  የጥፋተኝነት ብይን አሳልፏል ። ፍርድ ቤቱ ቴይለር በተመሠረቱባቸው 11 የወንጀል ክሶች ጥፋተኛ መሆናቸውን አሰታወቋል ። ቴይለር  በ 1990ዎቹ ሴራልዮን ውስጥ ይንቀሳቀስ ከነበረው የተባበሩት አብዮታዊ ግንባር ጋር በመመሳጠርና በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠውን የሴራልዮን መንግሥት እንዲወጋ በመርዳት  ነበር የተከሰሱት ። ተከታዩ የአንድሪ ሌስሊ ዘገባ የቻርልስ ቴይለርን የፍርድ ሂደት  ይቃኛል ።

Den Haag Ex-Präsident von Liberia Charles Taylor vor Gericht Monitor
ምስል AP

«ተካሳሹ፣ በተረጋገጠ ሁኔታ 11 የወንጀል ዓይነቶችን የሚመለከቱ ክሶች ናቸው የቀረቡባቸው። 5 ቱ በሰብአዊነት ላይ ወንጀል መፈጸማቸውን ነው የሚያወሱት። ይህ ደግሞ ፍርድ ቤቱ በተቋቋመበት ደንብ ፣ አንቀጽ 2 ፤ የሚያስቀጣ ነው። በተለይ ግድያ (በ 2 የክስ ሰነዶች ተወስቷል) አስገድዶ መድፈር (በ 4 የክስ  ሰነዶች ተጠቅሷል) የወሲብ ባሪያ ማድረግ የሚለው (5 የክስ ሰነዶች)፤ ሌሎች ኢሰብአዊ ድርጊቶች (8 የክስ ሰነዶች) ባሪያ ማድረግ ፣ (10 የክስ ሰነዶችን )የያዘ  ነው።»

Charles Taylor verhaftet
ምስል picture-alliance/dpa

የቀድሞው የላይቤሪያ መሬ ቻርልስ ቴይለር ጥፋተኝ የተባሉባቸውን ወንጀሎች  የዘረዘሩት የሄጉ ፍርድ ቤት  መሃል ዳኛ ሪቻርድ ሉስያክ እንደዘረዘሩት  ። በቴይለር ላይ የጥፋተኝነት ብይን የተሰጠባቸው እነዚህ ወንጀሎች እጎአ ከህዳር 1991 እስከ ጥር 2002 ዓም በተካሄደው የሴራልዮን የርስ በርስ ጦርነት ወቅት የተፈፀሙ ናቸው ። በወቅቱ አማፅያን  በሴራልዮን  ህዝብ ላይ እጆችና ጣቶችን መቁረጥ ጨምሮ  እጅግ ዘግናኝ  ወንጀሎች ፈፅመዋል ። ቴይለር በጎረቤት ሴራልዮን እጎአ ከ1991 እስከ 2001 በተካሄደው የርስ በርስ ጦርነት የሴራልዮኑን አማፂ ቡድን የተባበሩት አብዮታዊ ግንባርን በማስታጠቅ በማሰልጠንና በቁጥጥራቸው ሥር በማድረግ በምትኩ ደግሞ አልማዝ በመውሰድ ነወ የተወነጀሉት ። የቀድሞው አማፂ ቻርልስ ቴይለር እጎአ በ 1997 ነበር ተመርጠው ሥልጣን የያዙት ። በ2 ዓመቱ የላይቤሪያው የርስ በርስ ጦርነት ተቀሰቀሰ ። ቴይለር በ 2003 ወደ ናይጀሪያ ሲኮበልሉ የርስ በረሱ ጦርነተ አከተመ ። ከዚያን ጊዜ አንስቶ ናይጀሪያ ተሰውረው የቆዩት ቴይለር በ2006 ለሴራልዮን  ተላልፈው ተሰጡ ። ሆኖም  እዚያ መቆየታቸው

Charles Taylor verhaftet in Sierra Leone
ምስል dapd

አካባቢው እንዳይረጋጋ ያደርጋል ከሚል ፍራቻ ከፍሪታውን ሴራልዮን ወደ ሄግ እንዲዛወሩ ከተደረገ በኋላ የፍርዱ ሂደት ሰኔ 2007 ተጀመረ ። ከዚያን ጊዜ አንስቶ በርካታ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ፍርድ ቤት ተጠርተው ቀርበዋል ።  Open Society Justice Initiative  የተባለው የሰብዓዊ መብት  ድርጅት ባልደረባ ሴራልዮናዊ  ጠበቃ አልፋ ሴሳይ የፍርዱን ሂደት ታዝበዋል  ።

« ምንም እንኳን አቃቤ ህግ አንዳንድ ሰነዶችን በመረጃነት ቢወስድም ውስጥ አዋቂዎች የሰጡትን ምስክርነት ነው በዋነኛነት የተጠቀመው ። ይኽውም የቀድሞውን ምክትል ፕሬዝዳንት ጨምሮ በቴይለር የደህንነት ባለሥልጣን ውስጥ  ያገለገሉ ሰዎች ናቸው የመሰከሩባቸው ።  »

Den Haag Ex-Präsident von Liberia Charles Taylor vor Gericht
ምስል Reuters

የፍርዱ ሂደት በተለይ ታዋቂዋ ሞዴል እንግሊዛዊቷ ናኦሚ ካምፕ ቤል በምስክርነት ከቀረበች በኋላ  ዐብይ ዜና ሆነ ። ፍርድ ቤቱ ናኦሚን ለምስክርነት የጠራው ያረፈችበት ሆቴል ክፍል ድረስ ከቻርልስ ቴይለር የተበረከቱ አልማዞች  ተልኮላታል በመባሉ ነበር ። 3 ቱ ዳኞች የቀረቡትን መረጃዎች ተጨማሪ ጊዜ ወስደው ለማጣራት ና ውሳኔያቸውንም በፅሁፍ ለማቅረብ የፍርዱን ሂደት  የዛሪ ዓመት በመጋቢት ወር ለጊዜው አቋረጡት ።  ብይን ይጠበቅ የነበረው በታህሳስ አጋማሽ ላይ ቢሆንም ለዚህ ዓመት ለሚያዚያ ተቀጠረ ።  ሲሴይ እንደሚሉት በሴራልዮን አማፅያን የተፈፀሙትን ወንጀሎች ማረጋገጡ አያስቸግርም የአቃቤ ህግ ዋነኛው ተግባር ግን እነዚህን ወንጀሎች ከቴይለር ጋራ ማገናኘት ነበር ።

Prozess Charles Taylor Special Court for Sierra Leone
ምስል AP

« ሴራልዮን ሄደው አያውቁም ። አንዳንድ አዛዦቻቸው እና የሴራልዮን አማፅያንም  ወደ ላይቤሪያ መጓዛቸውና አምፅያኑም ወደ ሴራልዮን መመለሳቸውና እነዚህን ዘመቻዎች ማካሄዳቸው  ነው መረጃው ።  »

አልፋ ሲሴይ አሁንም ቢሆን የፍርዱ ሂደት ለወደፊት ዓለም ዓቀፍ የወንጀለኞች ጉዳዮች  ብርሃን ፈንጣቂ  ይሆናል  የሚል እምነት አላቸው ።

« በጣም ተዓማኒ የፍርድ ሂደት ነበር ። ምሳሌም ሆኗል ። ከፍተኛ ሥልጣን ያላቸው ሰዎች በኮሚሽኑ በወንጀል ከተከሰሱ ፣ ተጠያቂ እንደሚሆኑ ያሳያል ። »

ፍርድ ቤቱ በቴይለር ላይ የመጨረሻውን ቅጣት የሚያስተላልፈው ግንቦት 22 ፣ 2004 ዓም ነው ።

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ