1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በቫቲካን የኢትዮጵያ ጳጳሳዊ ኮሌጅ 100ኛ ዓመት ተከበረ

ሰኞ፣ ጥር 4 2012

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን መቀመጫ በሆነችው ቫቲካን የሚገኘው የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን ጳጳሳዊ ኮሌጅ 100ኛ አመት ተከበረ። ከኢትዮጵያና ከኤርትራ የተጓዙ ጳጳሳት፤ በጣልያን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዘነቡ ታደሰና የእምነቱ ተከታዮች ተገኝተዋል። ይኸው የጳጳሳት ማሰልጠኛ ኮሌጅ የተመሠረተው በጎርጎሮሳዊው 1919 ዓ.ም. ነበር

https://p.dw.com/p/3W88K
Vatikan Franziskus empfängt das Äthiopische Kolleg im Vatikan
ምስል Imago-Images/Independent Photo Agency/A. Giuliani

የተመሠረተው በጎርጎሮሳዊው 1919 ዓ.ም. ነበር

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን መቀመጫ በሆነችው ቫቲካን ከተማ የሚገኘው የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን ጳጳሳዊ ኮሌጅ 100ኛ አመት በትናንትናው ዕለት ተከበረ። ከኢትዮጵያ እና ከኤርትራ ወደ ቫቲካን የተጓዙ ጳጳሳት፤ በጣልያን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዘነቡ ታደሰ እና የእምነቱ ተከታዮች ተገኝተዋል። ይኸው የጳጳሳት ማሰልጠኛ ኮሌጅ የተመሠረተው በጎርጎሮሳዊው 1919 ዓ.ም. ነበር። በዓለም ካሉ ካቶሊካውያን አብያተ-ክርስቲያናት በቫቲካን እምብርት ኮሌጅ ያላት ኢትዮጵያ ብቻ ነች።  ተክለዕዝጊ ገብረየሱስ ይኸ "አስደናቂ እና የሚገርም ነው" ይላል።

Vatikan Franziskus empfängt das Äthiopische Kolleg im Vatikan
ምስል Imago-Images/Independent Photo Agency/A. Giuliani

ተክለዕዝጊ ገብረየሱስ

እሸቴ በቀለ

ኂሩት መለሠ