በሶማልያ የቀጠለው ውጊያ
ሐሙስ፣ ግንቦት 3 1998ማስታወቂያ
በሶማልያ መዲና ሞቃዲሾ በጦር አበጋዞች ኅብረት እና በሙሥሊም ሚሊሺያዎች መካከል ካለፈው እሁድ ጀምሮ የሚካሄደው ከባድ ውጊያ እስካሁን ቢያንስ የዘጠና ሰዎችን ሕይወት ማጥፋቱን የከተማይቱ ሐኪም ቤቶች አስታወቁ። ተፋላሚዎቹ ወገኖች፡ የብዙ ሰው ከተማይቱን እየለቀቀ እንዲሸሽ ያስገደደውን ውጊያቸውን እንዲያቆሙ፡ የተ መ ድ የሶማልያ ልዩ ልዑክ ፍራንስዋ ሎንሰኒ ፋል ጥሪ ቢያቀርቡም፡ ተማፅኖአቸው ሰሚ ጆሮ አለማግኘቱ ነው የተሰማው።