በሀዋሳ የመታሸግ ዕጣ የገጠማቸው ፋብሪካዎች
ማክሰኞ፣ ሐምሌ 27 2002ማስታወቂያ
ኢትዮዽያ ፤ማሽላና በቆሎ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የመጀመሯ ዜና ሲሰማ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የአውሮፓ ህብረት በቅርቡ 15 ሚሊዮን ዩሮ በድርቅ እና በርሀብ ለሚጎዱ ኢትዮጲያውያን እንዲውል፤ እርዳታ እንደሚሰጥ ማስታወቁ ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በቅርቡ በሀዋሳ ከተማ 10 ሺህ ኩንታል የእርዳታ ስንዴ በመጋዘናችሁ ተገኝቷል ተብለው፤ 10 ዱቄት ፋብሪካዎች ታሽገዋል። ፖሊስ እያጣራሁ ነው ይላል። ከተዘጋባቸው የዱቄት ፋብሪካ ባሌቤቶች አንደኛው ማሸጊያ ማዳበሪያው እንጂ ስንዴው የሀገር ውስጥ ነው ይላሉ። ልደት አበበ የሚመለከታቸውን አነጋግራ ተከታዩን ዘገባ አሰናድታለች።