ቁጣ የቀሰቀሰዉ ወሲባዊ ጥቃት በኢትዮጵያ
ሰኞ፣ ኅዳር 15 2007ማስታወቂያ
የ10ኛ ክፍል ተማሪ እና የ17 ዓመት ታዳጊ ነበረች። አዲስ አበባ ውስጥ ከአየር ጤና ወደ ጦር ኃይሎች ልትጓዝ በተሳፈረችበት ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ በነበሩ አምስት ሰዎች ታፍና ተወስዳ በተደጋጋሚ በመደፈሯ ለሞት የተዳረገችው-ሐና ላላንጎ። ታዳጊዋን አፍነው በመውሰድ ደፍረዋል በሚል የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው በምርመራ ላይ ናቸው። በሐና ላላንጎ ላይ የተፈጸመው ወሲባዊ ጥቃት በመገናኛ ብዙሃን ይፋ ከሆነ በኋላ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል።
ከነገ ጀምሮ ለ16 ቀናት የሚወሳዉ የጾታዊ ጥቃት ዘመቻ መክፈቻ ሥነ-ስርዓት ላይ ከተነሱ የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮች አንዱ በሐና ላላንጎ ላይ የተፈጸመው ወሲባዊ ጥቃት ነበር። በውይይቱ ላይ የተገኙት የታዳጊዋ ቤተሰቦች በሀዘን ተጎድተዋል ሲሉ የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ሃላፊ ወ/ሮ ዜናዬ ታደሰ ተናግረዋል።
ወሲባዊ ጥቃትን ጨምሮ ሴቶችን በተመለከቱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚሰራው የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር የህግ ድጋፍ ለሚፈልጉ የማማከር እና ድጋፍ አገልግሎት ይሰጣል። ማህበሩን በበላይነቲ የሚመሩት ወ/ሮ ዜናዬ ታደሰ በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት አሳሳቢ መሆኑንና ትኩረት እንደሚያሻው ተናግረዋል።
እሸቴ በቀለ
ተክሌ የኋላ