ስጋት ባጠላባት ኢትዮጵያ የምሁራን ሚና
እሑድ፣ መጋቢት 29 2011ማስታወቂያ
ለውጡ ብዙዎች ያልጠበቁት መሆኑ ብቻ ሳይሆን በተከታታይ አዎንታዊ ርምጃዎች በመታጀቡ የዓለም መገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስቦ ሰንብቷል። ተስፋና እፎይታው እንዳለ ሆኖ ለዓመታት ተዳፍኖ የቆየው የማንነት እና የወሰን ጥያቄ በዜጎች መካከል መገፋፋት እና መጋጨትን አስከትሎ በአራቱም አቅጣጫ ሞት እና መፈናቀል ማስከተሉ ስጋትን ማምጣቱ ይታያል። በዚህ መሃል በተለያዩ መድረኮችም ሆነ በማኅበራዊ መገናኛው የተማሩ የሚባሉ ወገኖች የሚሰነዝሯቸው ሃሳብ አስተያየቶች ውጥረቱን እያባባሰ ሀገር እንደሀገር የመቀጠሏን አሳሳቢ እያደረገው መምጣቱን ብዙዎች ይስማማሉ። DW ዶይቼ ቬለ እንዲህ ባለ ወቅት የምሁራን ሚና ምን መሆን አለበት ሲል እንግዶች ጋብዞ አወያይቷል። ሙሉ ውይይቱን ከድምፅ ዘገባው ያድምጡ፤
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ