1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስደተኞችን በመግደል የተጠረጠሩ መያዛቸዉ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 17 2006

በደቡባዊ ጣሊያን በሲሲሊ ግዛት የካታኒያ ከተማ ፖሊስ ከሊቢያ ወደጣሊያን ያቀኑ የነበሩ ስደኞችን የጫነች ጀልባ ዉስጥ ስደተኞችን ገድለዉ ባህር ዉስጥ በመወርወር የተጠረጠሩ አምስት ሰዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታዉቋል።

https://p.dw.com/p/1CiVH
Italien Flüchtlingsdrama Lampedusa Flüchtlingsboot
ምስል picture-alliance/ROPI

በጩቤ ተወግተዉና ተደብድበዉ ወደባህር የተወረወሩት ቁጥር ወደስልድሳ እንደሚጠጋ ጀልባዉ ዉስጥ የነበሩ የዓይን እማኞችን ዋቢ በማድረግ የገለፀዉ የካታኒያ ፖሊስ በደቡባዊ ላምፔዱዛ ከጀልባዉ ሞተር ከሚወጣዉ መርዛማ ጭስ የተነሳ መተንፈስ ሳይችሉ ቀርተዉ በመታፈን 29ሰዎችም መሞታቸዉንም አመልክቷል። ከስደተኞቹ የአንዱ ሕይወትም በካርቦን ሞኖክሳይድ ታፍኖ ወደሃኪም ቤት ሲወሰድ ማለፉም ተገልጿል።

ተኽለእዝጊ ገ/ኢየሱስ

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ