1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስዊድን ዉስጥ የኤርትራ መሪዎች ላይ ክስ መመሥረቱ፤

ሐሙስ፣ ሰኔ 26 2006

ኤርትራ ዉስጥ በእስር ላይ የሚገኘዉን የጋዜጠኛ ዳዊት ይስሐቅ ጉዳይ አስመልክቶ ከዚህ በፊት በአፍሪቃ የሰብዓዊ ጉዳይ ኮሚሽን ጥያቄያቸዉ እንዲታይላቸዉ ሲንቀሳቀሱ የቆዩ ሶስት የሕግ ባለሙያዎች በኤርትራ ባለስልጣናት ላይ ክስ አቀረቡ።

https://p.dw.com/p/1CVN6
Eritrea Präsident Isayas Afewerki
ምስል picture-alliance/dpa

የክስ ማመልከቻዉን ለፖሊስ ያቀረቡት ፔርሲ ብራት፣ የሱ ሳልካ እና የፓሪሱ ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች የሕግ ባለሙያ ፕሪስካ ኦርሶኖ ሲሆኑ፣ ክስ ያቀረቡት በኤርትራ ፕሬዝደንት እና ሚኒስትሮቻቸዉ ላይ ነዉ። ክሱ የቀረበዉ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂን ጨምሮ የሕግ፣ የመከላከያና የዉጭ ሚኒስትሮችና በፕሬዝደንቱ ልዩ አማካሪ ላይ መሆኑን የስቶክሆልም ወኪላችን ቴድሮስ ምህረቱ በላከዉ ዘገባ ገልጿል።

ቴድሮስ ምህረቱ

ሸዋዬ ለገሠ

ተክሌ የኋላ