1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት አስራ ስድስተኛ የገጠማቸው ተቃውሞ

ሐሙስ፣ ጥር 28 2001

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት አስራ ስድስተኛ በ 2 ተኛው የዓለም ጦርነት ስድስት ሚሊዮን አይሁዶች አልተጨፈጨፉም ፣ በወቅቱም ሰዎችን በመርዘኛ ጋዝ አፍኖ መግደያ ስፍራዎች አልነበሩም ሲሉ ለካዱት ጳጳስ ሪቻርድ ዊልያምሰን በቅርቡ ምህረት በማድረጋቸው ከየአቅጣጫው ተቃውሞ ተነስቶባቸዋል ።

https://p.dw.com/p/Go0x
ቤኔዲክት አስራ ስድስተኛምስል picture-alliance/ dpa

በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ካቶሊኮች መሪ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት አስራ ስድሰተኛ ውዝግብ ተለይቷቸው አያውቅም ። ጳጳሱ በተለያዩ አጋጣሚዎች በሚሰጧቸው አስተያየቶች ሙስሊሞችን ሴቶችን ፖላንዶችን ግብረ ሰዶማውያንና ሳንቲስቶችን አስቆጥተዋል ።