1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሕይወት እምሻው በፌስቡክ

ዓርብ፣ ጥር 29 2007

ሁላችንም ከልጅነት አንስቶ የምናስታውሳቸው ፤ አስቂኝ፤ አሳዛኝ ወይም አስገራሚ ገጠመኞች አሉን። እነዚህን ታሪኮች ግን ስንቶቻችን ዋጋ ሰጥተን፤ በቃላት አስውበን ወረቀት ላይ እናሰፍራቸዋለን። ከትምህርት ቤት ዘመኔ አንስቶ መፃፍ ያስደስተኝ ነበር የምትለው ሕይወት እምሻው፤ በትርፍ ጊዜዋ አጫጭር ታሪኮች እየፃፈች የብዙዎችን ትውስታ ቀስቅሳለች።

https://p.dw.com/p/1EW83
Hiwot Emishaw (Facebook) Screenshot
ምስል Hiwot Emishaw

አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኝ አንድ - ኤም ኤስ ኤች በሚባል መንግሥታዊ ባልሆነ ድርጅት ውስጥ የጤና ዘመቻ አስተባባሪ ሆና የምታገለግለው ሕይወት፤ ትርፍ ጊዜዋን የምታሳልፈው ድርሰቶችን፣አጫጭር ታሪኮችን በመፃፍ ነው።

የ 33 ዓመቷ ጎልማሳ - ሕይወት የፁሁፍ መንፈሱን ያገኘሁት ከአባቴ ነው ትላለች። ፌስ ቡክ ላይ ብዙ አንባቢዎች አሏት። « ነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከሕይወት እምሻው ጋር» ይላል የሕይወት እምሻው የፌስ ቡክ ገፅ፤ ከ 71 600 በላይ ሰዎች ገጿን ወደውላታል። በርካቶችም ከታሪኩ በታች አስተያየታቸውን ይገልፃሉ። ነገር ግን ሕይወት አንባቢዎቿን እጅጉን ያስደሰታቸው ታሪክ ይህ ነው ለማለት ያስቸግራል ትላለች።

Symbolbild Facebook Ausfall 27.01.2015
ምስል Reuters/D. Ruvic

ሕይወት እስካሁን የፃፈቻቸውን ታሪኮች በቁጥር አታውቃቸውም። ነገር ግን ረዝም የሚሉት እስከ 500 ይደርሳሉ ትላለች።

ሕይወት እምሻው እና በትርፍ ሰዓቷ የምትፅፋቸው አጫጭር ታሪኮች ጥቂቱን ከዚህ በታች በድምፅ ያገኙታል።

ልደት አበበ

አርያም ተክሌ