ለኢትዮጵያ የፍትህ ስርዓት ማሻሻያ የUSAID እገዛ
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 2 2011ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ የፍትህ ተቋማትን አቅም ለማጎልበት ይረዳል የተባለ ፕሮጀክት ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ይፋ ሆኗል። ለዚሁ ፕሮጀክት የዩናይትድ ስቴትስ የልማት ተራድኦ ድርጅት በምህጻሩ USAID አራት ሚሊዮን ዶላር እንደሚሰጥ ፕሮጀክቱ ይፋ በተደረገበት በሸራተን ሆቴል በተሰጠ መግለጫ ላይ ተነግሯል። የኢትዮጵያ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ ፕሮጀከቱ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያን የፍትህ ስርዓት ለማሻሻል ለተጀመሩ ስራዎች እገዛ እንደሚያደርግ ለዶቼቬለ DW በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ከአዲስ አበባ ዝርዝር ዘገባ አለው
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ