1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ለኞርዌዩ ነፍሰ ገዳይ የተሰጠው ብይን፤

ዓርብ፣ ነሐሴ 18 2004

የ 77 ሰዎችን ነፍስ ያጠፋው አንድ የቀኝ ጽንፈኛ ፤ ላይ በዛሬው ዕለት የ21 አመት እሥራት ፈረደ ። ፍርድ ቤቱ በዚሁ ውሳኔው ብሪይቪክ ዐዕምሮው የተነካ ነው ሲልም በይኗል ። ከብይኑ በኋላ የብሬቪክ ጠበቃ ነፍሰ ገዳዩ ንክ ስለተባለ ይግባኝ አይጠይቅም

https://p.dw.com/p/15wSK
Norwegian mass killer Anders Behring Breivik (C) arrives in the court room at Oslo Courthouse August 24, 2012. The Norwegian court delivers its verdict in the ten-week trial of gunman Breivik on Friday, deciding whether to send the anti-Muslim militant to jail or a mental hospital for the massacre of 77 people last summer. REUTERS/Heiko Junge/NTB Scanpix/Pool (NORWAY - Tags: CRIME LAW)
ምስል Reuters

አንድ የኖርዌይ ፍርድ ቤት ኖርዌይ ውስጥ ከአንድ አመት በፊት የ 77 ሰዎችን ነፍስ ያጠፋው አንድ የቀኝ ጽንፈኛ ፤ ላይ በዛሬው ዕለት የ21 አመት እሥራት ፈረደ ። ፍርድ ቤቱ በዚሁ ውሳኔው ብሪይቪክ ዐዕምሮው የተነካ ነው ሲልም በይኗል ። ከብይኑ በኋላ የብሬቪክ ጠበቃ ነፍሰ ገዳዩ ንክ ስለተባለ ይግባኝ አይጠይቅም ብለዋል ።የ33 አመቱ ቀኝ ፅንፈኛው ብሪይቪክ ዛሬ በንባብ የተሰማውን ብይን በፈገግታ ነበር ያዳመጠው ። ብሬይቪክ 10 ሳምንትት ለወሰደው ችሎት ራሱን እውሮፓን ከሙስሊሞች ወረራ ለመከላከል የሚዋጋ ሰሜነኛ አድርጎ እንደሚያይ ቃሉን ሰጥቷል ። ከግድያው ያመለጡ አንድ አንድ ወጣቶች በፍርድ ቤቱ ውሳኔ መደሰታቸውን አስታውቀዋል ። የታዛቢዎችም የተጎጂዎችም አስተያየት ምን እንደሆነ የአስክንዲኔቪያውን በተለይም የእሽቶክሆልሙን ዘጋቢአችንን ቴድሮስ ምህረቱን በስልክ ጠይቄው ነበር።

ቴድሮስ ምህረቱ

ተክሌ የኋላ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ