1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

"በርካታ ጉድለቶች እንዳሉ እናምናለን" -ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ

ሰኞ፣ መጋቢት 24 2010

የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢሕአዴግ ሊቀ-መንበር ዶክተር አብይ አሕመድን ጠቅላይ ምኒስትር አድርጎ ሾመ። የጠቅላይ ምኒስትሩን ሹመት ለምክር ቤቱ ያቀረቡት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው። የቀድሞው ጠቅላይ ምኒስትር በይፋ ሥልጣናቸውን ለአዲሱ ጠቅላይ ምኒስትር አስረክበዋል።

https://p.dw.com/p/2vMT7
Äthiopien Abiy Ahmed OPDO
ምስል Abdulbasit Abdulsemed

የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢሕአዴግ ሊቀ-መንበር ዶክተር አብይ አሕመድን ጠቅላይ ምኒስትር አድርጎ ሾመ። የጠቅላይ ምኒስትሩን ሹመት ለምክር ቤቱ ያቀረቡት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው። የቀድሞው ጠቅላይ ምኒስትር በይፋ ሥልጣናቸውን ለአዲሱ ጠቅላይ ምኒስትር አስረክበዋል።

ጠቅላይ ምኒስትር አብይ በምክር ቤቱ ባሰሙት ንግግር "በርካታ ጉድለቶች እንዳሉ እናምናለን" ሲሉ ተናግረዋል። "ወቅቱ ከስህተታችን ተምረን አገራችንን የምንክስበት ነው" ያሉት ጠቅላይ ምኒስትሩ የሕግ የበላይነትን ለማስፈን ቃል-ገብተዋል።

ጠቅላይ ምኒስትሩ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሻሻል እሰራለሁ ብለዋል። የኤርትራ መንግሥትም በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ልዩነት ለመፍታት እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል። 

እሸቴ በቀለ