1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፕሬዝደንት ኦባማ የኢትዮጵያ ጉብኝት

ሰኞ፣ ሐምሌ 20 2007

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋ ተነጋገሩ። ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ለገቡት የአሜሪካ ፕሬዝደንት ኢትዮጵያዊዉ አቻቸዉ ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ዛሬ ከቀትር በፊት በብሔራዊው ቤተ መንግሥት ሙሉ ወታደራዊ አቀባበል አድረገውላቸዋል።

https://p.dw.com/p/1G5RY
Äthiopien Barack Obama Hailemariam Desalegn PK
ምስል Getty Images/AFP/de Souza

ኦባማ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ዛሬ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫም ሀገሪቱ በአፍሪቃ ቀንድ በፀጥታ ረገድ ጉልህ ሚና እንደምትጫወት አመልክተዋል። ፕሬዚደንቱ በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰዉን ፅንፈኛ ቡድን አሸባብን ለመመከት ኢትዮጵያዊውያን ወታደሮች ስላሉ አሜሪካ ሠራዊት ማሠማራት እንደማያስፈልጋትም ገልጸዋል። ጋዜጣዊ መግለጫን የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ተከታትሎዋል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ልደት አበበ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ